ቀን 24/5/2015 ዓ.ም

“በኢትዮጵያ አዲስ ከተቀረጸው ስርዓተ ትምህርት ታንዛኒያ  ጠቃሚ ግብዓት አግኝታለች “የታንዛኒያ የትምህርት ፣ የሳይንስና የቴክኖሎጂ ቋሚ  ምክትል ሚኒስትር

የታንዛኒያ የትምህርት ፣ የሳይንስና የቴክኖሎጂ ሚኒስቴር  ልዑካን ቡድን  በትምህርት ሚኒስቴር የልምድ ልውውጥ ጉብኝት አድርጓል ።

12 አባላት ያሉት የታንዛኒያ የልዑካን ቡድን በቅድመ መደበኛ ፣ በሁለተኛ ደረጃ ፣ በቴክኒክና ሙያና በዩኒቨርስቲዎች በመዘዋወር ምልከታ አድርጓል።

ልዑካን ቡድኑን የመሩት የታንዛኒያ ሪፐብሊክ ቋሚ ምክትል የትምህርት፣ የሳይንስና የቴክኖሎጂ ሚኒስትር ፕሮፌሰር ጀምስ ኤፒፈን ጋብርኤል ሞድ  በጉብኝቱ ወቅት በኢትዮጵያ አዲስ ከተቀረጸው ስርዓተ- ትምህርት አገራቸው  በርካታ ጠቃሚ ልምዶችን እንዳገኘች ገልፀዋል።

በአሁኑ ወቅት አገራቸው ታንዛኒያ የስርዓተ ትምህርት ማሻሻያና ክለሳ ተግባራትን እያከናወነች መሆኑን የገለፁት ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ አዲሱ ስርዓተ ትምህርት  ለአገር በቀል ዕውቀቶች ፣ ለተግባርና ሙያ (ክህሎት) ትኩረት  የሰጠ መሆኑንን  ተናግረዋል።

በትምህርት ሚኒስቴር የስርዓተ ትምህርት ማበልጸጊያ መሪ ስራ አስፈጻሚ ቴዎድሮስ ሸዋርገጥ (ዶ/ር) በበኩላቸው ነባሩ ስርዓተ ትምህርት  መለወጥ ያስፈለገው በንድፈ ሀሳብ የታጨቀና የአገሪቱን ነባራዊ ሁኔታ ያላገናዘበ በመሆኑ ነው ማለታቸውን ትምህርት ሚኒስቴር ዘግባል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s