ቀን 21 / 3 / 2013 ዓ.ም

መረጃዎችን  በፍጥነት  ለማግኘት የዩቲዩብ ፣ የቴሌግራም ፣ የፊስቡክ እና  የትዊተር  ገፃችንን  ሰብስክራይብ  ያድርጉ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

ባልታጠበ  እጅ  አይንዎን  አፍዎን  እና  አፍንጫዎን  ባለመንካት  በዙሪያዎ  ላሉ  ሰዎች  አርአያ  ይሁኑ!

ቀን 4 / 3 / 2013 ዓ.ም

በትምህርት ቤቶች ለኮቪድ 19 በሽታ መከላከል  የሚውል የ1.5 ሚሊየን ብር የሚያወጣ የቁሳቁስ ድጋፍ መደረጉ ተገለፀ፡፡

ኮርዲያድ የተሰኘ ግብረ ሰናይ ደርጅት  ለተማሪዎች አገልግሎት  የሚውል  አንድ መቶ ሰማንያ ሺ  ለህጻናት እና 39 ሺ ለአዋቂ የአፍ እና አፍንጫ  መሸፈኛ ማስክ ፣ ዘጠና ስምንት  የሙቀት  መለኪያ  ማሽን እና ስድስት ሺ  ሳኒታይዘር ድጋፍ ማድረጉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ገልፅዋል፡፡ የቢሮው ሀላፊ አቶ ዘላለም ሙላቱ በቁሳቁስ ርክክቡ መርሃ ግብር ላይ ተገኝተው እንደገለፁት የ2013 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የብዙ አካላት ተሳትፎን በማካተት ሲሰራ መቆየቱን ጠቅሰው በዛሬው እለት ገብሬኤልዋ የህፃናትና ሴቶች በጎ አድራጎት ደርጅት አማካኝነት ኮርዲያድ በተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት ለተደረገው  ድጋፍ  በትምህርት ቢሮ እና በተማሪዎች ስም አመሰግናለሁ ብለዋል፡፡  

የገብሬኤልዋ የህፃናትና ሴቶች በጎ አድራጎት ደርጅት  ሀላፊ ቤዛ ሃይለማሪያም በበኩላቸው እንደገለፁት  ኮቪድ 19 ወረርሽኝ  በሽታ በአለም አቀፍ ደረጃ ለብዙ ሰዎች ህይወት  መጥፋትና ከፍተኛ ቀውስ ያስከተለ  ወረርሽኝ ነው ብለዋል፡፡ ህይወትን ከማጥፋት በሻገር  የትምህርት ሂደትን  በማስተጓጎል በርካታ ተማሪዎች እቤት እንዲቀመጡ በማድረጉና አሁን የተጀመረውን  የመማር ማስተማር  ስራ ለማገዝ በአንድ ነጥብ አምስት ሚለዮን ብር ወጪ የሚገመት የአፍ እና አፍንጫ  መሸፈኛ ማስክ፣የሙቀት  መለኪያ  ማሽን እና ሳኒታይዘር  ድጋፍ መደረጉን  በመግለጽ በድርጅታቸዉ ጥያቄ መሰረት ኮርዲያድ ግብረ ሰናይ ደርጅት ድጋፉን በመስጠቱ  ድርጅቱ ሊመሰገን ይገባል ብለዋል ፡፡ አክለውም  ከትምህርት ቢሮ ጋር በጋራ የመስራትና ለተማሪዎች የሚደረገው  ድጋፍ  ተጠናክሮ  ይቀጥላል ብለዋል፡፡

መረጃዎችን  በፍጥነት  ለማግኘት የዩቲዩብ ፣ የቴሌግራም ፣ የፊስቡክ እና  የትዊተር  ገፃችንን  ሰብስክራይብ  ያድርጉ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

ባልታጠበ  እጅ  አይንዎን  አፍዎን  እና  አፍንጫዎን  ባለመንካት  በዙሪያዎ  ላሉ  ሰዎች  አርአያ  ይሁኑ!

የ2013 የትምህርት ዘመን ጥቅምት 30 ቀን 2013 ዓ.ም ይጀመር የነበረው የገጽ ለገጽ የመማር ማስተማር ሂደት ላልተወሰነ ጊዜ ተራዘመ፡፡



ቀን 27 / 2 / 2013 ዓ.ም
 
የ2013 የትምህርት ዘመን ጥቅምት 30 ቀን 2013 ዓ.ም  ይጀመር የነበረው የገጽ ለገጽ የመማር ማስተማር ሂደት  ላልተወሰነ ጊዜ ተራዘመ፡፡
 
ለክልላዊ እና ብሄራዊ ፈተና ተፈታኝ የሆኑ  የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን የክለሳ ትምህርት ግን ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
 
በአዲስ አበባ ከተማ የ2013 የትምህርት ዘመን ተማሪዎችን ለኮቪድ-19  ወረርሽኝ በማያጋልጥ ሁኔታ ጥቅምት 30 ቀን 2013 ዓ.ም ትምህርት ለመጀመር በርካታ የቅድመ ዝግጅት  ስራዎች  በማከናወን ላይ መሆኑ ይታወሳል፡፡
 
ከ8ኛ እና 12ኛ ክፍል ውጪ በተቀሩን ክፍሎች ትምህርት  ከመጀመሩ በፊት በኮቪድ-19 የቀውስ ጊዜ የትምህርት አመራርና አስተዳደር ስትራቴጂ እቅድ ላይ የተቀመጡ ስታንዳርዶችን ሟሟላት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ አስፈላጊ ዝግጅቶች በተሟላ ደረጃ እስኪጠናቀቁ ድረስ በከተማዋ ለመጀመር የታቀደው  የገጽ ለገጽ  ትምህርት ላልተወሰነ ጊዜ የተራዘመ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
 
ከባለፈው ጥቅምት 16 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ መሰጠት የጀመረው  የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል የገጽ ለገጽ የክለሳ ትምህርት የመማር ማስተማር ሂደት  ግን ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
 
መረጃዎችን  በፍጥነት  ለማግኘት የዩቲዩብ ፣ የቴሌግራም ፣ የፊስቡክ እና  የትዊተር  ገፃችንን  ሰብስክራይብ  ያድርጉ!
 
You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ
 
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
 
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
 
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
 
ባልታጠበ  እጅ  አይንዎን  አፍዎን  እና  አፍንጫዎን  ባለመንካት  በዙሪያዎ  ላሉ  ሰዎች  አርአያ  ይሁኑ!