ቀን 17/6/2014 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አዲሱን ስርዓተ ትምህርት መሰረት አድርጎ ተዘጋጅቶ በተመረጡ ትምህርት ቤቶች በሙከራ ደረጃ ተግባራዊ በመደረግ ላይ ያለዉን የተማሪዎች የመማሪያ መጽሀፍና የመምህር መምሪያን ለሚገመግሙ መምህራን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ ፡፡

የመጽሀፍ ግምገማው ከዛሬ ጀምሮ ለአንድ ሳምንት ከተለያዩ ትምህርት ቤቶች በውጤታቸውና ስነ-ምግባራቸው በተመረጡ መምህራንና በቢሮው ስርዓተ ትምህርት ዝግጅትና ትግበራ ባለሙያዎች በአማርኛ እና አፋን ኦሮሞ ቋንቋዎች በየትምህር አይነቱ በእቴጌ መነን አዳሪ ትምህርት ቤት እስከ ምሽቱ 4 ሰሃት ድረስ እንደሚካሄድ ከወጣው መርሀ- ግብር ለማወቅ ተችሉዋል ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ዘላለም ሙላቱ በመርሀ-ግብሩ ተገኝተው በመጽሀፍ ግምገማው ለሚሳተፉ መምህራን ባስተላለፉት መልዕክት  መምህራኖች በዚህ ታሪካዊ በሆነው የትውልድ ግንባታ ሂደት የበኩላቸውን አሻራ ማሳረፍ በመቻላቻው ከፍተኛ ኩራት ሊሰማቸው እንደሚገባ ገልጸው በመጽሀፍ ዝግጅቱ ከመተርጎም ጀምሮ ለሙከራ ትግበራ እስኪደርስ ኃላፊነታቸውን ለተወጡ አካላት በሙሉ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

ኃላፊው አክለውም የግምገማው ተሳታፊዎች መጽሀፍቱ በሙከራ ደረጃ ሲተገበሩ የነበሩ ጠንካራና መስተካከል ያለባቸውን ጉዳዮች በአግባቡ በመለየት እንዲሁም በሁለተኛ መንፈቅ አመት በሙከራ ደረጃ ተግባራዊ  የሚደረጉትን ይዘቶች  በዝርዝር በማየት ወደ ሙሉ ትግበራ ለመግባት በሚደረገው እንቅስቃሴ የበኩላቸውን ኃላፊነት ሊወጡ እንደሚገባም አስገንዝበዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ አድማሱ ደቻሳ በበኩላቸው አዲሱን ስርዓተ ትምህርት መሰረት አድርጎ የተዘጋጀው የተማሪዎች የመማሪያ መጽሀፍም ሆነ የመምህር መምሪያ ወደ አማርኛ እና አፋን ኦሮሞ ቋንቋዎች ከመተርጎም ጀምሮ በተለያዩ ባለድርሻ አካላት በማስገምገም በ44 አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በሙከራ ደረጃ ተግባራዊ መደረጉን ገልጸው በአዲስ አበባ ደረጃ ከዚህ ተግባር ጋር በተገናኘ የተከናወኑ ተግባራት ለተለያዩ  ክልሎች ጭምር እንደተሞክሮ እየተወሰዱ እንደሚገኝ በመግለጽ በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በአዲስ አበባ ደረጃ መጽሀፍቱ ታትመው ወደ ሙሉ ትግበራ እንዲገቡ ለማስቻል የቅድመ ዝግጅት ስራ እየተሰራ እንደሚገኝም አስረድተዋል፡፡

የቢሮው የስርዓተ ትምህርት ዝግጅትና ትግበራ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሩ አቶ ጌታቸው ታለማ እና የአፋን ኦሮሞ ስርዓተ ትምህርት ዝግጅት ትግበራና አጠቃላይ ሱፐርቪዝን ዳይሬክቶሬት ባለሙያው አቶ ገመቺስ ፍቃዱ ገምጋሚዎቹ መጽሀፍቱን ይዘት በሚገመግሙበት ወቅት ሊከተሉዋቸው በሚገቡ አሰራሮች ዙሪያ ገለጻ አድርገዋል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 16/6/2014 ዓ.ም

የ2013 ዓ.ም 12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ፡፡

በተለያዩ ሀገራዊ ምክንያቶች ተራዝሞ የቆየው የ2013 ዓ.ም 12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ይፋ መሆኑን ሀገር አቀፍ የትምህርት ምዝናና ፈተናዎች ኤጀንሲ አስታወቀ።

በመጀመሪያ ዙር የተሰጠው የ12ኛ ክፍል የስነዜጋና ስነምግባር ትምህርት የፈተና ውጤት ለዩኒቨርስቲ መግቢያ መወዳደሪያነት እንዳያገለግል መወሰኑንም ኤጀንሲው ገልጿል።

ተማሪዎችም ከዛሬ ጀምሮ ውጤታቸውን ማየት እንደሚችሉ ጠቁሟል።

የፈተና እርማቱ ደህንነታቸው አስተማማኝ በሆኑና ከንክኪ ነጻ በሆኑ የማረሚያ ማሽኖች አስፈላጊው የደህንነት ጥበቃ በፌደራል ፖሊስና በሴኩሪቲ ካሜራዎች ታግዞ በጥንቃቄ መከናወኑንም ነው የገለጸው።

ከዚህ በተጨማሪም የፈተናዎች ውጤት በትምህርት ዓይነት፣በትምህርት ቤትና በተማሪ ደረጃ ሰፊ የውጤት ትንተና በማካሄድ የእያንዳንዱ የትምህርት ዓይነት ውጤት ተገምግሟል ብሏል ኤጀንሲው ባወጣው መግለጫ።

በዚሁ መሰረት በመጀመሪያው ዙር (ከጥቅምት 29 እስከ ህዳር 02/2014 ዓ.ም) በተሰጠው የስነዜጋና ስነምግባር ፈተና በሁሉም ትምህርት ቤቶች በሚባል ደረጃ የውጤት መመሳሰልና ግሽበት ስለታየበት የፈተና ውጤቱ ለዩኒቨርሲቲ መግቢያ መወዳደሪያነት እንዳያገለግል መወሰኑንም ጠቅሷል።

በሌሎቹ የትምህርት ዓይነቶች የተገኘው የውጤት ትንተና ሲታይ ምንም ዓይነት ችግር እንደሌለበትም ተገልጿል።

ስለሆነም ተማሪዎች የሚከተሉትን አማራጮች በመጠቀም ውጤታቸውን ማወቅ ይችላሉ።

1) በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዌብሳይት፡- result.neaea.gov.et

2) በትምህርት ሚኒስቴር ድረገፅ፡- result.ethernet.edu.et

3) በቴሌግራም ቦት (Telegram Bot):- @moestudentbot – በዚህ ማስፈንጠሪያ በመግባትና Exam Result የሚለውን በመጫን በመልዕክት መጻፊያው ላይ የመለያ ቁጥራቸውን በማስገባት እና የ ምልክት በመጫን መላክና ውጤታቸው ማየት ይችላሉ።

4) በ9444 የ ኤስ ኤም ኤስ (9444 SMS) ፡- በመልክት ማስተላለፊያ መጻፊያ ላይ የመለያ ቁጥራቸውን በማስገባት ወደ 9444 በመላክ ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ።

በውጤት ላይ ቅሬታ ያላቸው ተማሪዎች result.neaea.gov.et በመግባት እና Compliant የሚለውን በመጫን ቅሬታቸውን በፎርሙ ላይ በመሙላት ማቅረብ ይችላሉ ተብሏል።

በ2013 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ሊሰጥ የነበረው የ12ኛ ክፍል ፈተና በተለያዩ ሀገራዊ ምክንያቶች ወደ 2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ተሸጋግሮ በሁለት ዙር መሰጠቱ ይታወቃል።

የመጀመሪያው ዙር ከጥቅምት 29 እስከ ህዳር 02/2014 ዓ.ም ለወንድ 293 ሺህ 865 ሴት 250 ሺህ 703 ድምር 544 ሺህ 568 ተማሪዎች ተሰጥቷል።

ከፀጥታ ችግር ጋር ተያይዞ በመጀመሪያው ዙር ሳይፈተኑ ለቀሩ ለወንድ 27 ሺህ 979 ሴት 26 ሺህ 456 ድምር 54 ሺህ 435 ተማሪዎች ደግሞ ከጥር 24-27/2014 ዓ.ም በሁለተኛው ዙር ፈተና እንዲወስዱ ተደርጓል።

በአጠቃላይ በሁለቱም ዙር ከተመዘገቡት 617 ሺህ 991 ተማሪዎች ውስጥ ወንድ 321 ሺህ 844 ሴት 277 ሺህ 159 ድምር 599 ሺህ 003 (96.9%) ተማሪዎች ፈተናውን መውሰድ ችለዋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 14/6/2014 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ትምህርት ቴክኖሎጂ ትግበራ ዳይሬክቶሬት የኢንፎረሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ቡድን በየትምህርት ቤቱ ለሚገኙ የአይ ሲቲ ባለሙያዎች በተግባር የተደገፈ ስልጠና በመስጠት ላይ መሆኑን አስታወቀ፡፡

ስልጠናው በዋናነት በስኩል ኔት መሰረተ ልማት አጠቃቀምና ተዛማጅ ርዕሰ ጉዳዮችን መሰረት አድርጎ በቢሮው የአይ ሲቲ ባለሙያዎች እየተሰጠ እንደሚገኝ የአጠቃላይ ትምህርት ቴክኖሎጂ ትግበራ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሩ አቶ በለጠ ንጉሴ ገልጸዋል፡፡

ዳሬክተሩ አክለውም ስልጠናው በየትምህርት ቤቱ በሁለተኛው መንፈቅ አመት ተማሪዎች የፕላዝማ ትምህርትን ጨምሮ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ትምህርት መማር እንዲችሉ ሰልጣኞቹ ከፍተኛ ኃላፊነት እንዳለባቸው ገልጸው እስካሁን በአምስት ክፍለከተሞች ከሚገኙ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ የአይሲቲ ባለሙያ ዎች ስልጠናውን መውሰዳቸውን ጠቁመው በቀጣይ ቀሪ ክፍለከተሞችም ተመሳሳይ ስልጠና እንደሚሰጣቸው አስታውቀዋል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 14/6/2014 ዓ.ም

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያዉ መንፈቅ ዓመት የማጠቃለያ ፈተና መሠጠት ተጀመረ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በ2014 የትምህርት ዘመን በተዘጋጀዉ የትምህርት ሴሌዳ መሰረት የመጀመሪያዉ መንፈቅ ዓመት የማጠቃለያ ፈተና በሁሉም የቅድመ አንደኛ ፣ የአንደኛ እና አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ የመንግስትና የግል ትምህርት ቤቶች ላይ መሰጠት ጀምራል፡፡

ፈተናዉ ከዛሬ ከየካቲት 14 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ እስከ የካቲት 18 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ ቆይታ የሚያደርግ ሲሆን ተማሪዎች መልካም የፈተና ጊዜ ቆይታ እንዲሆንላችሁ እየተመኘን በጥሩ ስነ-ምግባርና በራስ መተማመን ፈተናዉን በመውስድ ለላቀ ውጤት ተግታችሁ ልትሰሩ ይገባል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ…

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 11/6/2014 ዓ.ም

7ኛውን አለም አቀፍ የሚጥል ህመም ምክንያት በማድረግ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የስርአተ ፆታ ማካተትና ማስረፅ ዳይሬክቶሬት ከኬር ኢፕልፕሲ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር የሚጥል ህመም ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ ::

የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ም /ቢሮ ኃላፊ አቶ አድማሱ ደቻሳ በስልጠናው መክፈቻ ባደረጉት ንግግር የሚጥል ህመምና ሌሎች መሰል ህመሞች በትምህርት ስርዓቱ ላይ የራሱ የሆነ መጥፎ አሻራ የሚያደርስ በመሆኑ ህመሙን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ቢሮው አብሮ እንደሚሰራ ተናግረዋል :: የስልጠናው ታሳታፊዎችም በቂ ግንዛቤ ወስደው ተማሪዎችና የትምህርት ማህበረሰቡን ማገዝ እንደሚገባቸው አሳስበዋል::

የኬር ኤፕሊፕሲ መስራችና ዳይሬክተር የሆኑት ወ/ሮ እናት የእውነቱ በስልጠናው የሚሳተፉ የጤና ባለሞያዎች በትምህርት ቤት ውስጥ ለሚያጋጥሙ ችግሮች ድጋፍ በማድረግ ሕፃናትን ለፍሬ ለማድረስ አቅም እንደሚሆኑ ገልፀዋል:: ወ/ሮ እናት አክለዉም ስልጠናው የሚጥል ህመም ያለባቸው ሰዎች በህክምና በመታገዝ የሕይወት አላማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ግንዛቤ ለማስጨበጥ የተዘጋጀ እንደሆነ ተናግረዋል ::

በእለቱ የጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ነርቭ ሀኪም የሆኑት ዶክተር መስከረም ዳኛቸው የሚጥል በሽታ ምንነትና መንስኤ ፣ ምልክቶች ፣ የመጀመሪያ እርዳታ አሰጣጥና መሰል ጉዳዮች ላይ ግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት ሰጥተዋል ::

በስልጠናው ከተመረጡ100 ትምህርት ቤቶች የመጡ የጤና ባለሞያዎች ተሳታፊ ሆነዋል ::

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 11/6/2014 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ለቢሮው ሰራተኞች በመንግስት ሰራተኞች አዋጅ ቁጥር 56/2010 ዙሪያ  ስልጠና መስጠት መጀመሩን አስታወቀ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ቢሮ ጋር በመተባበር ለቢሮው ሰራተኞች ስልጠና መስጠት መጀመሩን ያሳወቀ ሲሆን  ስልጠናው በዋናነት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በወጣው የመንግስት ሰራተኞች አዋጅ ቁጥር 56/2010 ዙሪያ ሰራተኞች በቂ ግንዛቤ ይዘው እና መብትና ግዴታቸውን አውቀው ስራቸውን በአግባቡ መስራት እንዲችሉ ታስቦ መዘጋጀቱን የቢሮው የሰው ሀብትአስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሩ አቶ ብዙነህ በቀለ ገልጸው አዋጁ በዋናነት ስለ ከባድና ቀላል የዲሲፒሊን ቅጣቶች፤ የአመት እረፍት አሰጣጥና ያለ ደሞዝ እረፍት አወጣጥን የተመለከቱ እና ሌሎች ዝርዝር ጉዳዮችን እንዳካተተ አስረድተዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሲሳይ እንዳለ በስልጠናው መክፈቻ ባስተላለፉት መልዕክት ሰራተኛው አዋጆችን እና መመሪያዎችን በአግባቡ ተገንዝቦ ስራውን መስራት ከቻለ ውጤታማ መሆን እንደሚችል ጠቁመው በዚህ ስልጠናም ተሳታፊ የሆኑ ባለሙያዎች እስካሁን ያከናወኑዋቸው ተግባራት ከመመሪያና ደንብ አንጻር ምን እንደሚመስሉ እንዲሁም በቀጣይ ጊዜያትም ስራቸውን እነዚህኑ መመሪያዎች እና አዋጆችን ተከትለው መስራት እንዲችሉ እነደሚረዳቸውም አስታውቀዋል ፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 9/6/2014 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ተግባረ ዕድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ 200,000 የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ማስክ ለትምህርት ቤቶች ድጋፍ አደረገ።

የማስኩ ርክክብ በኮሌጁ ቅጥር ግቢ ውስጥ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ዘላለም ሙላቱ፣የልደታ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አሰግድ ሀይለገብርኤል ፣ የኮሌጁ ዲን አቶ ግሩም ግርማን ጨምሮ የትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊዎች ፣ የኮሌጁ ምክትል ዲኖች፣አሰልጣኝ መምህራንና ተማሪዎች በተገኙበት ተካሂዷል።

በርክክብ መርሀ ግብሩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ዘላለም ሙላቱ እንዳስታወቁት የአዲስ አበባ ተግባረ ዕድ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በርካታ ባለሙያዎችን ያፈራ አንጋፋ ተቋም መሆኑን ጠቅሰው ለተማሪዎቻችን ለአጠቃቀም ምቹ  በሆነ መልኩ ያዘጋጀውን ማስክ በማበርከቱ ከፍተኛ ምስጋና እንደሚገባው በመግለጽ በቀጣይ ጊዜያትም ኮሌጁ ለትምህርት ሴክተሩ መሰል ድጋፎች ማድረጉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል  እምነታቸው መሆኑን አስገንዝበዋል።

የልደታ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አሰግድ ሀይለገብርኤል በበኩላቸው ኮሌጁ ወጣቶች ሙያዊ ክህሎት ኖሯቸው በተለያዩ የስራ መስኮች እንዲሰማሩ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ገልጸው የኮቪድ ወረርሽኝ በተማሪዎች ላይ የሚያደርሰውን አደጋ ለመከላከል ይህን የመሰለ ድጋፍ ማድረጉ ለሌሎች ተቋማት አርአያ እንደሚያደርገው አስታውቀዋል።

ኮሌጁ ተማሪዎችን የማሰልጠን ተግባር ባሻገር በተለያዩ ማህበረሰቡን ተጠቃሚ በሚያደርጉ ተግባራት እንደሚሳተፍ የኮሌጁ ዲን አቶ ግሩም ግርማ ገልጸው በዛሬው እለት በኮሌጁ አቅም የተዘጋጁ እና ለትምህርት ቢሮ የተረከቡ 200,000 ማስኮች 680,000 ብር እንደሚገመቱ አስረድተዋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 4/6/2014 ዓ.ም

የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ትምህርት ጽ/ቤት ስር በሚገኙ የመንግስት እና የግል ት/ቤቶች መካከል ልምድ ልውውጥ ተደረገ።

የልምድ ልውውጡ በአብዩት ፋና ትምህርት ቤት እና በግል ት/ቤቶች ርዕሳነ  መምህራን  መካከል ተደርጓል።

በፕሮግራሙ ላይ የክፍለ ከተማው የት/ት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አደፍርስ ኮራ ፣ የወረዳ 10 የብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ሀይሉ እና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት በአብዩት ፋና ትምህርት ቤት የልምድ ልውውጡ ተካሄዳል።

በልምድ ልውውጡ ላይ አቶ አደፍርስ ኮራ እንደገለጹት ተማሪዎች በትምህርታቸው ውጤታማ እንዲሆኑ ከተማሪ ወላጆችና ባለድርሻ አካላት ጋር መስራት እንደሚያስፈልግ ገልጸው በቀጣይም የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የሚረዱ ስራዎችን በጋራ መስራትና የልምድ ልውውጥን በማጠናከር ለተማሪዎች ውጤት መሻሻል ብሎም ለሀገር ተተኪ ትውልድ ለመፍጠር ተባብረን መስራት ይገባል ብለዋል።

በልምድ ልውውጡ የቤተ ሙከራ ፣የሙዚቃ ማዕከሎች፣የትምህርት ቤት ምድረ ግቢ ንፅህና አያያዝ እንዲሁም በትምህርት ቤቱ የመረጃ አያያዝ ላይ ግብኝት ተደርጋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 4/6/2014 ዓ.ም

የመምህር ያሬድ እና የተማሪ ናትናኤል የፈጠራ ስራዎች

የመምህር ያሬድ እና የተማሪ ናትናኤል በልደታ ክፍለ ከተማ በወረዳ 10 ትምህርት ፅህፈት ቤት ስር የሚገኘዉ የአፍሪካ ህብረት አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህር እና ተማሪ ናቸዉ፡፡

በትምህርት ቤቱ የፊዚክስ መምህር የሆነዉ ያሬድ የቶርኖ ማሽን ለመስራት ችላል፡፡

በተግባር ስራዉ በትምህርት ቤቱ የሚታወቀዉ መምህር ያሬድ የሰራዉ የፈጠራ ስራ ለተለያዩ ስራዎች ቅርፅ ማውጫነት ፣የተለያዩ ፑሊዎችን እና ልዩ ልዩ ስራዎችን ለመስራት የሚያስችል ነው።

በሌላ መልኩ የኒውተን ሰርድ ሎው ፊዚክስ ትምህርት ለፈጠራ ስራዉ እንዳገዘዉ የተናገረዉ የ9ኛ ክፍል ተማሪ የሆነዉ ናትናኤል እራስን ለመከላከል የሚያገለግል መሳሪያ በመስራት እና የሰራዉ መሳሪያ በተግባር አገልግሎት እንደሚሰጥ ለማሳየት ችላል፡፡ 

ለተሰሩት እንዲሁም ቀጣይ ለሚሰሩት የፈጠራ ስራዎች የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር አቶ ሰለሞን ይታየው ከጎናቸዉ መሆናቸውን እና በተሰረዉ ስራ መደሰታቸውን በመግለጽ አበረታተዋቸዋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 1/6/2014 ዓ.ም

በአዲስ አበባ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ሞዴል ፈተና እየተሰጠ ነው።

የሞዴል ፈተናው በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ የመንግስትና የግል ትምህርት ቤቶች 8ኛ እና 12ኛ ክፍል ለሚማሩ ተማሪዎች የተዘጋጀ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዲናኦል ጫላ ገልጸው ፈተናውም በክልላዊ እና ሀገር አቀፍ ደረጃ በሚፈተኗቸው የትምህርት አይነቶች መዘጋጀቱን አስታውቀዋል።

ዳይሬክተሩ አክለውም የ8ኛ ክፍል ሞዴል ፈተናው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ መዘጋጀቱን እና የ12ኛ ክፍል ፈተና ደግሞ ክፍለ ከተሞች እንዲያዘጋጁ መደረጉን አስገንዝበዋል።

በ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በአዲስ አበባ ከ73,000 ሺ በላይ ተማሪዎች የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ይወስዳሉ ተብሎ እንደሚጠበቅና 47,000 ሺ የሚሆኑ ተማሪዎች ደግሞ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ለመውሰድ ዝግጅት በማድረግ ላይ እንደሚገኙ  ከስራ ክፍሉ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!