ቀን 22/4/2015 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ ቡድን የኢ ስኩል (e-school ) ሲስተም  ሶፍትዌርን ከሚያለማው ድርጅት ጋር በጋራ በመሆን ስልጠና ሰጠ።

ስልጠናው የኢ ስኩል (e-school)ሲስተም  ሶፍትዌር በሙከራ ደረጃ ተግባራዊ ከሚደረግባቸው የ1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ ርዕሳነ መምህራን ሱፐርቫይዘሮችና ጉዳዩ ለሚመለከታቸው የትምህርት ባለሙያዎች የተሰጠ ሲሆን ስልጠናውም ትሪያ ሶሊሽን/TRIA SOLUTION/ በተሰኘውና ሶፈትዌሩን በማልማት ላይ ከሚገኘው ካምፓኒይ በመጡ የዘርፉ ባለሙያዎች ነው የተሰጠው፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳኘው ገብሩ በስልጠናው መክፈቻ ባስተላለፉት መልዕክት  ስልጠናው የኢ -ስኩል ሲስተሙ ሶፍትዌሩን  በአግባቡ ተግባራዊ በማድረግ የትምህርት አገልግሎቱን ዘመናዊና በቴክኖሎጂ የታገዘ እንዲሆን በማሰብ መዘጋጀቱን  ገልጸው የስልጠናው ተሳታፊዎችም ሶፍትዌሩን ከሚያለማው ድርጅት በመጡ ባለሙያዎች ከሶፍትዌሩ አተገባበር ጋር በተገናኘ የሚሰጠውን ገለጻ መሰረት በማድረግ በየትምህርትቤቶቻቸው ተግባራዊ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የትምህርት ቴክኖሎጂ ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ በለጠ ንጉሴ በበኩላቸው ስልጠናው በዋናነት ሶፍትዌሩ በሙከራ ደረጃ ትግባራዊ ከሚደረግባቸው 20 የሚሆ ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ ርዕሳነ መምህራን ሱፐርቫይዘሮችና ጉዳዩ ለሚመለከታቸው የትምህርት ባለሙያዎች መዘጋጀቱን ጠቁመው ስልጠናውም  ከሶፍትዌሩ አተገባበርና አጠቃቀም ጋር በተገናኘ በቂ ግንዛቤ በመፍጠር የትምህርት ስርአቱ በቴክኖሎጂ የታገዘ ማድረግን ታሳቢ አድርጎ መዘጋጀቱን አስረድተዋል፡፡

የኢ-ስኩል ሲስተሙ በስሩ የተለያዩ ንዑሳን ሲስተሞች እንዳሉትና ሲስተሙም በዋናነት የወረቀት ስራን በመቀነስ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የትምህርት አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መሆኑን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ ቡድን መሪው  አቶ ደረጀ ዳኜ  ገልጸው በቀጣይ  ሶፍትዌሩን ከሚያለማው ካምፓኒ ጋር በጋራ በመሆን የመማር ማስተማር ሂደቱንም ሆነ የትምህርት መረጃ አያያዝ ስርአቱን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሰራ አስታውቀዋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ቀን 22/4/2015 ዓ.ም

የተማሪ ወላጆች በብዝሀ ቋንቋ አተገባበር ጥናት ላይ ተወያዩ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ በሁሉም ክፍለ ከተሞች የሚገኙ የተማሪ ወላጆች ከአፍ መፍቻ ተጨማሪ የሀገር ውስጥና የውጪ ቋንቋዎችን በትምህርት ስርዓቱ ለማካተት የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርስቲ ባደረገው የብዝሀ ቋንቋ አተገባበር ጥናት ላይ ተወያይተዋል።

የብልፅግና ፓርቲ አዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መለሰ ዓለሙ በየክፍለ ከተማው በውይይቱ ለተሳተፉ የተማሪ ወላጆች በቪዲዮ ኮንፈረንስ ባስተላለፉት መልዕክት ኢትዮጵያ ብዝሀነቷን አክብራና ተንከባክባ ከትውልድ ትውልድ እንድትሸጋገር የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን አንስተዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ የትምህርት ስርዓቱ በዋናነት ሊተገብረው የሚገባው ጉዳይ ለነገው ትውልድን የማነፅና የሀገር ግንባታ እንዲሁም ለልጆቻችን የተሻለች ሀገርን መፍጠር ነው ሲሉ ተናግረዋል::

ለብዝሀ ቋንቋ አተገባበር ኮተቤ ዩኒቨርስቲ ያደረገው ጥናትም ህብረብሔራዊ አንድነታችንን ለማጠናከር የራሱ ድርሻ እንደሚኖረው በማስረዳት ወላጆች የሚሰጧቸው ሀሳቦች ለብዝሀ ቋንቋ አተገባበሩ እና ለመማር ማስተማሩ ሂደት ስኬታማነት እንደ ተጨማሪ ግብአት እንደሚወሰዱ አቶ መለሰ ተናግረዋል።

የብዝሀ ቋንቋ አተገባበርን የጥናት ውጤት ያቀረቡት የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርስቲ መምህር ዶ/ር ዮሴፍ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች በጥናቱ ወቅት ግብአት መስጠታቸውን ገልፀው የዛሬው ውይይትም ከቅርበት፣ ከተደራሽነት፣ ከተጠቃሚነት እንዲሁም ከማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና አስተዳደራዊ ጉዳዮች አንፃር የጥናቱ ውጤት ምን እንደሚመስል ከወላጆች ጋር የጋራ ለማድረግና በተጨማሪ ግብአት ለማዳበር መሆኑን አስረድተዋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ቀን 21/4/2015 ዓ.ም

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በ2015 የትምህርት ዘመን የ6ኛ፣ የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል የመጀመሪያ ሴሚስተር ሞዴል ፈተና በዚህ መርሀ ግብር መሰረት ከሰኞ ከ24/4/2015 ዓ.ም ጀምሮ የሚሰጥ በመሆኑ ተማሪዎች ተገቢውን ዝግጅት በማድረግ ፈተናውን እንድትወስዱ አናሳውቃለን!

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ቀን 21/4/2015 ዓ.ም

በብዝሀ ቋንቋ ዙርያ በተጠና የጥናት ውጤት ላይ ውይይት ተደረገ፡፡

የጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር አመራሮች በብዝሀ ቋንቋ ዙርያ በተጠና የጥናት ውጤት ላይ ውይይት አደረጉ።

ለብዝሀ ቋንቋ አተገባበር ከአፍ መፍቻ ቋንቋ በተጨማሪ የሀገር ውስጥና የውጪ ቋንቋዎችን በስርዓተ ትምህርት ለማካተት የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርስቲ ባደረገው የጥናት ውጤትም  ላይ ውይይት ተደርጓል።

ብዝሀ ቋንቋ ማወቅ የህዝብ ፍላጎት ቢሆንም የአለም አቀፍና የሀገር ውስጥ ልምምድን ማየትና በጥናት መመለስ አስፈላጊ በመሆኑ የከተማ አስተዳደሩ ሀላፊነት ወስዶ ለሀገር ግንባታ የሚጠቅም ስራ እየሰራ መሆኑን ማሳያ እንደሆነ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ ገልጸዋል።

በተመሳሳይ የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ተስፋዬ ኦሜጋም ብዝሀ ቋንቋ ማወቅ ለአለም ሰው ልጆች ሁሉ በጣም አስፈላጊ ነው ብልጽግና ፓርቲ ሰው ተኮር በመሆኑ ፍላጎቱን ለማሟላት የሚሰራ መሆኑን ማሳያ ነው።ጥናቱ እየገነባን ላለነው ሁሉን አቃፊ የበለጸገች ኢትዮጵያ አስፈላጊ ውጤት ይዞ የመጣ መሆኑንና አመራሩ ለተግባራዊነቱ የራሱን ሚና መወጣት እንደሚገባው መግለጻቸውን ከጉለሌ ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ የሳያል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ቀን 21/4/2015 ዓ.ም

ሳምንታዊ የጽዳት ዘመቻ በዳግማዊ ሚኒሊክ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተካሄደ፡፡

“ቆሻሻን መጣል ይብቃ“ በሚል መሪ ሀሳብ የመማሪያ አካባቢን ጽዱና ውብ የማድረግ ተግባርን ዓላማ ያደረገ የጽዳት ዘመቻ በዳግማዊ ሚኒሊክ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተካሄደ፡፡

በመርሀ ግብሩ ክፍሌንና ትምህርት ቤቴን አጸዳለሁ! ፤ ውብና ጽዱ በሆነ ትምህርት ቤት እማራለሁ! ፤  ጽዳት ህይወቴ ነው!፤ ጽዳት ጤናዬ ነው!  እና ሁላችንም ቆሻሻን ባለመጣል የመማሪያ ቦታዎቻችንን ንጽህና እናስጠብቅ የሚሉ መልዕክቶችን የትምህርት ቤቱ ተማሪዎች ማስተላለፋቸውን ከክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያሳያል፡፡  

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ቀን 18/4/2015 ዓ.ም

በብዝሀ ቋንቋ ዙርያ በተጠና  የጥናት ውጤት ላይ ውይይት ተደረገ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች አስተዳደሩ ለብዝሀ ቋንቋ አተገባበር ከአፍ መፍቻ በተጨማሪ የሀገር ውስጥና የውጪ ቋንቋዎችን በስርዓተ ትምህርት ለማካተት የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርስቲ ባደረገው የጥናት ውጤት ላይ ውይይት ተደርጓል።

የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ጥናቱ ከባለፈው ዓመት መጋቢት ወር ጀምሮ ሲደረግ መቆየቱን ጠቅሰው በተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በውይይት እየዳበረ መሆኑን አስረድተው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮችም በግልፀኝነት ተወያይተውበት  በቀጣይ ህዝቡን ማወያየት እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል::

የጥናት ፅሁፉን ያቀረቡት የኮተቤ ዩኒቨርስቲ መምህር ዶ/ር ዮሴፍ ከአንድ በላይ ቋንቋዎችን ማወቅ ከሚያስገኘው ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ በተጨማሪ ማህበራዊ መስተጋብርንና ትስስርን የማጠናከር እና ሌሎች ፍልስፍናዊና ባህላዊ እውቀቶችን እንደሚያጎናፅፍ፤ በአገራችንም በተለይም ኦሮሚያ ክልል ከሌሎች ክልሎች ጋር በሚዋሰንባቸው አካባቢዎችና በሌሎችም ክልሎች የተጀማመሩ ስራዎች ያስገኟቸውን መልካም ውጤቶች በመጥቀስ አብራርተዋል።

በተደረገው ጥናት ከአገር ውስጥ ቋንቋዎችና ከእንግሊዝኛ በተጨማሪ ከቅርበት ከተደራሽነት እና በሌሎች ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ምክንያቶች ሌሎች የአካባቢው ቋንቋዎችንም ለመማር ምርጫቸው መሆኑ በጥናቱ መረጋገጡ ቀርቧል።

ጥናቱ የተማሪዎችን፣ የመምህራንንና የወላጆችን ሀሳብ ያካተተ ለምሁራን ቀርቦ በተጨማሪ ግብዓት የዳበረና በቀጣይም የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችም በውይይታቸው የበለጠ የሚያዳብሩት መሆኑ ተገልጿል።

በውይይቱ የተሳተፉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አመራሮችም  ለብዝሀ ቋንቋ አተገባበር ከአፍ መፍቻ በተጨማሪ የሀገር ውስጥና የውጪ ቋንቋዎችን  መማር የጥናት ውጤትም መሬት ላይ ያለውን እውነታ ያረጋገጠ መሆኑንና  የቀጣዩ ትውልድ ማህበራዊ ትስስር የበለጠ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ብዝሀ ቋንቋ  አተገባበር ፋይዳው የጎላ መሆኑንም አስረድተዋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ቀን 15/4/2015 ዓ.ም

የ2015 ዓ.ም የውስጥ ስፖርታዊ ውድድር በእቴጌ መነን የልጃገረዶች አዳሪ ት/ቤት ተጀመረ፡፡

በስፖርታዊ ውድድሩ አጀማር ስነ-ስርዓት ላይ የት/ቤቱን ማህበረሰብ በስፖርታዊ የውድድር ፕሮግራሞች አማካኝነት የእርስ በእርስ ግንኙነትን ወዳጅነትንና አንድነትን እንዲያጠናክር ንቁ ጤናማና ውጤታማ ማህበረሰብ እንዲሆኑ የስፖርታዊ ፕሮግራሞች ማስፈፀሚያ ማንዋል በማዘጋጀት በ2013 ዓ.ም ወደ ትግበራ የተገባ መሆኑ ተገልጻል፡፡

በስፖርታዊ ውድድሩ የት/ቤቱ እና የአቻ ት/ቤት አመራሮች፤ መምህራንና ተማሪዎች ታድመዋል፡፡

በዚህ ስፖርታዊ ውድድር ስነ-ስርዓት ላይ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የእቴጌ መነን የልጃገረዶች አዳሪ ት/ቤት ርዕሰ መምህርት ወ/ት ሃና ፀጋዬ የስፖርታዊ ውድድሮች ጤናማ ማህበረሰብ ለመፍጠር የሚጫወቱት ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የገላን የወንዶች 2ኛ ደረጃ አዳሪ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር አቶ ካሳሁን መርጋለተወ ዳዳሪ መምህራንና ተማሪዎች መልካም የውድድር ጊዜ ተመኝተዋል፡፡

በዚህ ስፖርታዊ ውድድር መምህራንና የተማሪዎች በሁለት ምድብ የሚሳተፉ ሲሆን እያንዳንዱ ምድብ በስሩ የቮሊቮል፤ የእግር ኳስ፤ የእሩጫ፤ የቴብል ቴንስ እና የገመድ ጉትቻ ውድኖች ይኖሩታል፡፡

በመክፈቻ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ልዩ ልዩ ስፖርታዊ ትዕይንቶች በተማሪዎች የቀረቡ ሲሆን በዕለቱ የመጀመሪያው ውድድር የሆነው በካኔኑስ እና በሉሲ የሴት ተማሪዎች የእግር ኳስ ቡድኖች መካከል የተደረገው ውድድር ነው፡፡ 

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ቀን 14/4/2015 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የስርአተ ጾታ ማስረጽና ማካተት ዳይሬክቶሬት የፀረ ጾታዊ ጥቃት ጥቃት ቀን ወይም የነጭ ሪቫን ቀንን የቢሮው ሰራተኞት በተገኙበት አከበረ።

ቀኑ ዘንድሮ ሴትን አከብራለሁ ጥቃቷንም እከላከላለሁ በሚል መሪ ቃል በአለም አቀፍ ደረጃ ለ31ኛ እንዲሁም በሀገራችን ደግሞ ለ17ኛ ጊዜ ከህዳር 16 ጀምሮ በተለያዩ መርሀ ግብሮች ሲከበር መቆየቱ ተገልጿል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሲሳይ እንዳለ በመርሀ ግብሩ ባስተላለፉት መልዕክት ቀኑ ሴቶች ላይ የሚደርስን ጥቃት ለመከላከል በማሰብ በተለይም በወንዶች የሚከበር እንደመሆኑ በሴቶች ላይ የሚደርስ ማን ኛውንም ጥቃት በመከላከል የሀገርን ሁለንተናዊ እድገት ማስቀጠል እንደሚገባ ጠቁመው የትምህርት ማህበረሰቡም ሆነ ጉዳዩ የሚመለከተው ማን ኛው ባለድርሻ አካል በትምህርት ተቋማት የሚስተዋሉ ጾታዊ ጥቃቶችን ለመከላከል በሚደረገው እንቅስቃሴ የበኩላቸውን ኃላፊነት መወጣት እንደሚጠበቅባቸው አስረድተዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የስርአተ ጾታ ማስረጽና ማካተት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወይዘሮ አበባ ዘውዴ በበኩላቸው የነጭ ሪቫን ቀን እ.አ.አ ታህሳስ 1989 ዓ.ም ካናዳ ሞንትሪያል ከተማ በአንድ ወጣት ወንድ 14 ሴት ተማሪዎችን አስከፊ በሆነ መልኩ መገደላቸውን መሰረት በማድረግ እ.አ.አ ከ19 91ዓ.ም ጀምሮ ወንዶች ሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን በመቃወም የሚከበር መሆኑን ገልጸው ጾታዊ ጥቃትን ከመከላከል አንጻር የወንዶች ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ጥቃቱን ማውገዝና መከላከል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

በመርሀ ግብሩ ማጠቃለያ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳኘው ገብሩ ባስተላለፉት መልዕክት ቀኑ ሴቶች ላይ የሚደርስ ማንኛውንም ጥቃት ከአስተሳሰብ ጀምሮ በማውገዝና በመከላከል ተግባራዊ እንቅስቃሴ ማድረግ እንደሚገባ አስታውቀዋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ…

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ቀን 14/4/2015 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ዛሬ ባካሄደው 8ኛ  መደበኛ ስብሰባ ከሃምሌ 2014 ጀምሮ በኮተቤ የትምህርት ዩንቨርሲቲ ሲጠና በቆየው የብዝሃ ቋንቋ ስርዓተ ትምህርትን ለመወሰን በተደረገው  ጥናት ላይ ዝርዝር  ውይይት አድርጓል፡፡

ለቀጣይም ከዘርፉ ባለሙያዎች ፤ ከባለድርሻና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ተደርጎበትና ተጨማሪ ግብዓት ተወስዶበት የብዝሃ ቋንቋ ስርዓተ ትምህርቱ ለውሳኔ ይቀርብ ዘንድ አቅጣጫ ሰጥቶበታል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ቀን 12/4/2015 ዓ.ም

በአዲስ አበባ ከተማ ባሉ አንዳንድ ትምህርት ቤቶች ተከስቶ የነበረው የፀጥታ ችግር ተረጋግቶ የመማር ማስተማሩ ሂደት በሰላም እየተከናወነ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡

ባለፈው ሰሞን በአንዳንድ ትምህርት ቤቶች ላይ ባንዲራና መዝሙርን ሽፋን በማድረግ  አጋጥሞ የነበረው የፀጥታ ችግር ተቀርፎ የመማር ማስተማሩ ሂደት በሠላም እየተከናወነ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል ፡፡

መምህራን ፣ ወላጆች እና በየደረጃው የሚገኙ የትምህርት ቤት አመራሮችን በልዩ ልዩ መድረኮች ማወያየት በመቻሉ እና የፀጥታና የደህንነት የጋራ ግብረ ሀይሉ ከልዩ ልዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ባከናወነው  የተቀናጀ ሥራ በትምህርት ቤቶች ላይ አጋጥሞ የነበረውን የፀጥታ ችግር መቅረፍ እንደተቻለ ገልጿል ፡፡

በትምህርት ቤቶች ውስጥ ዘላቂ ሰላም ለማምጣት ለልዩ ልዩ አካላት ከሚሰጠው የግንዛቤ ማስጨበጫ  ሥራ ጎን ለጎን የመማር ማስተማሩ ሂደት ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ እንዲቀጥል ህግ የማስከበር ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉን  የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልፆል፡፡

ባለፈው ጊዜ አጋጥሞ በነበረው የፀጥታ ችግር ላይ ድብቅ አጀንዳቸውን ለማራመድ ሲንቀሳቀሱ በተገኙ አካላት ላይም በህግ አግባብ እርምጃ የተወሰደ ሲሆን በስሜት በመነዳት እና ባለማወቅ የፀረ-ሰላም ኃይሎች መጠቀሚያ የሆኑ አብዛኛው ተማሪዎች አስፈላጊው ምክር ተሰጥቷቸው መለቀቃቸውን ተገልፆል፡፡

ሰላምና ደህንነትን የማስጠበቅ ኃላፊነት ለፀጥታ አካላት ብቻ የሚተው ተግባር ባለመሆኑ ህብረተሰቡ ህገ-ወጥ ድርጊት ሲያጋጥም ፈጥኖ ጥቆማ የመስጠት ልምዱን አጠናክሮ እንዲቀጥል እና ፀረ-ሰላም ኃይሎች ተማሪዎችን የአጀንዳቸው ማራመጃ እንያዳደርጓቸው ወላጆች ልጆቻቸውን መከታተል፣ መምከርና መቆጣጠር እንዳለባቸው የአዲስ አበባ ፖሊስ መልእክቱን አስተላልፏል፡፡

የፀጥታ አካላት የህብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት የማረጋገጥ ኃላፊነት እንዳለባቸው ፖሊስ አስታውቆ ግጭትን የፖለቲካ ትርፍ ማሳኪያ መንገድ በማድረግ የህብረተሰቡን አብሮነት የሚሸረሽሩ ተግባራት ላይ የተሰማሩ ፀረ-ሰላም ኃይሎች ሁኔታዎች በተረጋጉበት እና የመማር ማስተማሩ ሂደት ሰላማዊ በሆነ ሁኔታ እየተካሄደ ባለበት  በአሁኑ ወቅት  የታሰሩ ተማሪዎች አልተለቀቁም የሚል የተዛቡ መረጃዎችን እያሰራጩ ነው፡፡

በታችኛው ፍ/ቤት በዋስ እንዲፈቱ የተወሰነላቸውን ግለሰቦች መብትን ፖሊስ የማክበር ግዴታ ያለበት ቢሆንም በህጉ መሰረት የስር ፍ/ቤት በሰጠው የዋስትና ጉዳይ ላይ ይግባኝ የማለት ኃላፊነት እንዳለው እየታወቀ ፖሊስ የፍ/ቤትን ትእዛዝ አላከበረም የሚል መረጃ በአንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያዎች መሰረጨቱ ተገቢ አለመሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ እያስታወቀ አሁንም  የሚመለከታቸውን አካላት ሳይጠይቁ የተዛባ መረጃ የሚያሰራጩ አካላት ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ ይገባል ብሏል፡፡

በልዩ ልዩ መንገዶች የትምህርት ቤቶችን ፀጥታ ለማደፍረስ በሚንቀሳቀሱም ሆነ በተለይ የተዛባ ሀሰተኛ መረጃ የሚያሠራጩ አካላት ላይ የአዲስ አበባ ፖሊስ  እያደረገ  ያለውን ጥብቅ ቁጥጥር በማጠናከር አጥፊዎችን ህግ ፊት የማቅረብ ተግባሩን አጠናክሮ  እንደሚቀጥል አስታውቋል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/