ቀን 20/5/2014 ዓ.ም

የየካ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽፈት ቤት ከ1.5 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የግብዓት ድጋፍ ለመርሳ 2ኛ ደ/ት/ቤት  አደረገ::

የየካ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽፈት ቤት በሰሜን ወሎ ዞን ለሚገኘዉ እና በጦርነቱ ምክንያት የወደመዉን መርሳ 2ኛ ደ/ት/ቤት ለማቋቋም እንዲቻል ከ1.5 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የግብዓት ድጋፍ አድርጋል፡፡

ጽፈት ቤቱ በስሩ ከሚገኙ ከ7ቱ 2ኛ ደ/ት/ቤቶች ያሰባሰበዉን ከ1.5 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ግብአት ድጋፍ ማድረጉን አሳውቃል::

ድጋፋን የሀብሩ ወረዳ ት/ፅ/ቤት ሀላፊ፣ የመርሳ 2ኛ ደ/ት/ቤት ር/መምህራን፣ መምህራንና ተማሪዎች በተገኙበት ከየካ ክ/ከተማ ት/ፅ/ቤት የድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴዎች ተረክበዋል::

የድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴዉ ት/ቤቱ  ሙሉ በሙሉ የወደመ መሆኑን ፣ የላብራቶሪ ፣ አይሲቲ ፣ የቤተ መፅሀፍት፣ የፕላዝማ  እና ሌሎችም ግብዓቶች ሙሉ ለሙሉ መዘረፉቸዉን እና መውደማቸዉን መመልከቱን ገልጻል::

የሀብሩ ወረዳ ትምህርት ጽፈት ቤት ሀላፊ እና ማህበረሰቡ ቀደም ሲል ትምህርት ቤቱን ለማቋቋም ምንም አይነት ድጋፍ እንዳልተደረገ በመግለጽ ለችግራችን ቀድሞ ለደረሰዉ ለየካ ክ/ከተማ አስተደዳር ት/ፅ/ቤት እና ለ2ኛ ደ/ት/ቤቶች ምስጋና ካቀረቡ በሀላ አሁን በተደረገላቸዉ ድጋፍ ትምህርት ቤቱን ትምህርት ለማስጀመር እንደሚችሉ ማሳወቃቸዉን ከየካ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽፈት ቤት ያገኘነዉ መረጃ ያሳያል::

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ…

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 20/5/2014 ዓ.ም

“ኩረጃ በቃ!”  ንቅናቄ ተጀመረ፡፡

የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ትምህርት ፅ/ ቤት በ2014 ዓ.ም የተማሪዎችን ስነምግባርና ውጤት ለማሻሻል ከጀመረው ስራ አንዱ የሆነውን “ኩረጃ በቃ!” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ የንቅናቄ መድረክ የክፍለ ከተማው 1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች በተገኙበት በዛሬዉ እለት አስጀምሯል፡፡

የንቅናቄ መድረኩን በመክፈቻ ንግግር ያስጀመሩት የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሽታዬ መሃመድ ተማሪዎች ቀጣይ ሃገር ተረካቢ እንደመሆናችሁ ሃገራችሁ እናንተን ለማገዝ ሰፊ ስራዎች እየሰራች እንደሆነ በመገንዘብ በጥሩ ውጤትና ስነ-ምግባር ኩረጃን በመጠየፍ ሃላፊነታችሁን እንድትወጡ አሳስባለሁ ብለዋል ፤ በመድረኩ  የተገኙ ተማሪዎችም ኩረጃን በማጥፋት አርአያነታቸውን እንዲያሳዩ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡

የክፍለ ከተማው ትምህርት ጽ/ ቤት ኃላፊ ወ/ሪት ሳምራዊት ቅባቱ በበኩላቸው የንቅናቄ መድረኩ መከፈት በ2014 ዓ.ም የታቀደው የተማሪዎች ውጤትና ስነምግባር ለማሻሻል ተግባር አንዱ ክፍል እንደሆነ ገልጸው፤ ተማሪዎች ከዚህ ንቅናቄ መድረክ በኋላ የስነምግባር ክፍተት ያለባቸውን ተማሪዎች የማረምና የማብቃት ከፍተኛ ሃላፊነት እንዳለባቸው ተናግረዋል ፡፡

ትምህርት የተማሪዎችን እውቀት፤ክህሎትና አመለካት በማሳደግ ስብእናን ለማነጽ የሚያስችል የአንድ ሃገር ትልቅ መሳሪያ በመሆኑ እኩይ ስነምግባርና ኩረጃን መጠየፍ የተማሪዎች ልምድ እንዲሆን በውይይቱ ወቅት ተነስቷል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ…

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 18/5/2014 ዓ.ም

የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት በ2014 በጀት ዓመት ባለፉት ስድስት ወራት ያከናወናቸውን አበይትና ቁልፍ ተግባራትን ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ገመገመ።

የክፍለ ከተማው ትምህርት ጽ/ቤት በተያዘው በጀት ዓመት ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ በትምህርት ተደራሽነትና ጥራት ፣በተማሪዎች የምገባ ፕሮግራም፣ እንዲሁም በመማር ማስተማሩ ሂደት ዙሪያ ያከናወናቸውን ዋና ዋና ተግባራት የክፍለ ከተማና የክላስተር ሱፐርቫይዘሮች፣ር/መምህራንና መምህራን፣የትምህርት ጽ/ቤት አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በዛሬው ዕለት የውይይት መድረክ አካሄዷል።

የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፋ አቶ አለልኝ ወንዴ ተቋሙ በ2014 በጀት ዓመት ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ያከናወናቸውን አበይትና ቁልፍ ተግባራት ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን በተለይም ጽ/ቤቱ በክፍለ ከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ የመንግስትና የግል ትምህርት ቤቶች ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲኖር፣ ተማሪዎች በእውቀትና በስነ-ምግባር ታንፀው የነገ ሃገር ተረካቢ ዜጋ  እንዲሆኑ ለማስቻል እንዲሁም በትምህርቱ ዘርፍ ተጠያቂነት ያለው አሰራር ከመዘርጋት ጋር በተያያዘ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ዘርፈ ብዙ ስራዎች  መከናወናቸውን በሪፖርቱ አመላክተዋል።

በክፍለ ከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ የመንግስት የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤቶች ከተማሪዎች የምገባ ፕሮግራም፣ የዩኒፎርምና የደብተር ድጋፍ በበጀት ዓመቱ መደረጉን የገለፁት ኃላፊው ተቋሙ ከመደበኛ ስራው ጎን ለጎን  እንደ ሃገር የገጠመንን ፈተና በአሸናፊነት ለመወጣት የትምህርት ማህበረሰቡን በማስተባበር ለጀግናው የመከላከያ ሰራዊት ከ7 ሚሊዮን ብር  በላይ  ሃብት በማሰባሰብ ድጋፍ ከማድረግ ባሻገር ተማሪዎችንና መምህራንን በማስተባበር የዘማች አርሶ አደሮችን ሰብል የመሰብሰብ ስራ መሰራቱንም አቶ አለልኝ ወንዴ አያይዘው ተናግረዋል።

ጽ/ቤቱ ባለፉት ስድስት ወራት ያከናወናቸውን ዋና ዋና ተግባራት ባለድርሻ አካላት በተገኙበት መገምገሙ ተቋሙ ለትምህርት ጥራትና ተደራሽነት ያለውን ቁርጠኝነት ያሳየ ነው ያሉት ተሳታፊዎች በተያዘው በጀት ዓመትም ተቋሙ  ከመማር ማስተማር ፣በሁሉም ትምህርት ቤቶች ተጠያቂነትና ወጥነት ያለው አሰራር ከመዘርጋት እንዲሁም  ከባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅቶ ከመስራት ጋር በተያያዘ አበረታች ስራዎች መሰራታቸውን ገልፀው  ጽ/ቤቱ ከተማሪዎች ስነ-ምግባር  እና በአንዳንድ ትምህርት ቤቶች ላይ የሚስተዋለውን  የፍሳሽ ማስወገጃ እና ሌሎች ተያያዥ ችግሮችን ተቋሙ በቀጣይም ሊፈታ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

በመጨረሻም ለተነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያ እና ምላሽ ከመድረክ መሰጠቱን ከክፍለ ከተማዉ ትምህርት ጽፈት ቤት ያገኘነዉ መረጃ ያሳያል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 18/5/2014 ዓ.ም

የልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት የመጀመሪያ 6 ወራት የስራ አፈፃፀም ከባለድርሻ አካላት ጋር ገመገመ፡፡

የክፍለ ከተማዉ ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሪት እጅጋየሁ አድማሱ በመክፈቻ ንግግራቸዉ በመጀመሪያ 6 ወራት ከክ/ከተማ እስከ ትምህርት ቤት ድረስ በርካታ ስራዎች መሰራታቸዉን ፤ ከመማር ማስተማሩ ስራ ጎን ለጎን ሃገራችን ኢትዮጵያ የገጠማትን ትልቅ ፈተና ለመወጣት እንደ ትምህርት ሴክተር ለመከላከያ ሠራዊት ደም በመለገስና የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ፣ እንዲሁም ለተፈናቀሉ ወገኖች የቁሳቁስ፣ የገንዘብ እና የደረቅ ምግቦች ድጋፍ መደረጉን አስታውሰው “ዘመቻ በትምህርት ልማት ሠራዊት” በሚል መሪ ቃል ከክ/ከተማ እስከ ት/ቤት ድረስ ሠፊ ንቅናቄ በማድረግ የትምህርት ማህበረሠቡ የ”NoMore” እንቅስቃሴ ላይ የበኩሉን ሚና እንዲወጣ ተደርጓል ብለዋል፡፡ በመቀጠልም ከንፋስ ስልክ እና ከኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ወደ ልደታ ክ/ከተማ የመጡ ተቋማትን እንኳን ደህና መጣችሁ ለማለት ኬክ በጋራ ቆርሰዋል፡፡

የትምህርት መረጃ አመራር ስርዓት ቡድን መሪ በሆኑት አቶ መንግስቱ አሳቦ በመጀመሪያ 6 ወራት ከቁልፍ እና ከአበይት ተግባራት አንፃር የተሠሩ ስራዎች ሪፖርት አቅርበዋል፡፡ በሪፖርቱ በአማራጭ መሠረታዊ  እና ጎልማሶች ትምህርት ዙሪያ ፣ በት/ት ጥራት አሃድ ፣ በተ.ወ.ማ [ተማሪ፣ ወላጅ ማህበር] እና በመምህራን ማህበር የተሠሩ ስራዎች፣ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለይቶ ከመፍታት አንፃር የተከናወኑ ተግባራት ፣ የት/ት ሽፋን ተደራሽነት፣ በህብረተሠብ ተሳትፎ የተሠበሠበ የሃብት መጠን፣ በ6ቱ መርሃ ግብሮች የተሠሩ ስራዎች፣ ከ8ኛ እና ከ12ኛ ክፍል ውጤት ማሻሻያ ልዩ ዕቅድ አንፃር የተተገበሩ ስራዎች እንዲሁም ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ቀርቧል፡፡

በመጨረሻም በቀረበው ሪፖርት ላይ ከተሳታፊዎች ለተነሱ አስተያየቶች እና ጥያቄዎች ከመድረክ መሪዎች ምላሽ ተሠጥቷል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 17/5/2014 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2014 ዓ.ም ትምህርት ዘመን የ6 ወራት እቅድ አፈፃፀምን ከቢሮ ሰራተኞች ጋር ገመገመ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳምሶን መለሰ በመክፈቻ ንግግራቸው እንዳሉት በዝግጅት ምእራፍ በ2013 በጀት ዓመት የታዩ ጥንካሬዎች ለማስቀጠል በ2014 አይቀጥሉም ተብለው የተቀመጡ ጉድለቶችን ለማረም አቅደን የገባን በመሆኑ በአፈፃፀም የተደረጉ ጥረቶች የተሻሉ ነበሩ ብለዋል :: አቶ ሳምሶን አክለዉም የተገኙ ውጤቶች ከቢሮ እስከ ትምህርት ቤት ባሉ አካላት የጋራ ርብርብና ጥረት የተገኘ ነው ብለዋል ::

በዕለቱ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2014 ዓ.ም ትምህርት ዘመን የ6 ወራት እቅድ አፈፃፀም ከሶስት ዋና አላማዎችና አስራ ዘጠኝ ዋና ዋና ግቦች አንፃር በየዳይሬክቶሬቱ የተከናወኑ ተግባራት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት በእቅድና በጀት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በሆኑት በአቶ ጌታሁን ለማ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል::

በሪፖርቱ በግማሽ ዓመት እንደ ቢሮ የተከናወኑ ዋና ዋና ሥራዎች ያጋጠሙ ችግሮችና የመፍትሄ ሃሳቦች እንዲሁም በበጀት ዓመቱ ቀሪ ወራት ሊከናወኑ የሚገቡ የትኩረት አቅጣጫዎች ቀርበዋል  ::

የቀረበውን ሪፖርት መሰረት በማድረግ ያልተካተቱ ነጥቦች ማብራሪያ የሚፈልጉ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ከተሳታፊዎች ተነስተዉ ምላሽ ተሰጥቷቸዋል ::

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 16/5/2014 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ የስርአተ ጾታ ማስረጽና ማካተት ዳይሬክቶሬት ፆታዊ ጥቃትን መሰረት ያደረገ ስልጠና ሰጠ፡፡

በስልጠናው መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የስርአተ ፆታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ አበባ ዘውዴ እንዳሉት ትምህርት ቤቶች ከመማር ማስተማር ጎን ለጎን በትምህርት ቤት ማሻሻል መርሃ ግብርና በራስ አቅም ጾታን መሰረት ያደረገ ጥቃትን ለመከላከል የተሻለ አፈፃፀም ያላቸውን ት/ቤቶች ልምድ ለሌሎች በማሳየት ልምድ ለመስጠት እንደሚያግዝ ተናግረዋል፡፡

ፆታዊ ጥቃትን ለመከላከል በሁሉም ክፍለ ከተሞች እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን በተመለከተ የተሰበሰበ ቼክ ሊስት ውጤት እንደሚያሳየው አሁንም በበቂ ሁኔታ የወንዶችና ሴቶች መፀዳጃ አለመለየትና ምቹ አለማድረግ እንዲሁም የሴቶች የንፅህና መጠበቂያና በወር አበባ ጊዜ እረፍት ለሚፈልጉ ተማሪዎች የተዘጋጀ ማረፊያ አለመኖርና የመሳሰሉ ችግሮች እንደሚታዩ የገለፁት የሥርአተ ፆታ ባለሙያዋ ወ/ሮ ትእግስት በሪሁን በስልጠናው የሚሳተፉ የተሻለ አፈፃፀም ያላቸው ክበባት ሀላፊዎች በክትትልና ድጋፍ የታዩ ክፍተቶችን ለመሸፈንና ዝቅተኛ አፈፃፀም ያሳዩ ትምህርት ቤቶችን ለማብቃት እድል እንደሚሰጣቸው ተናግረዋል፡፡

ስልጠናዉ ፆታዊ ጥቃትን ከመከላከል ረገድ ዝቅተኛ አፈጻፀም የታየባቸው ት/ቤቶችን ለመደገፍ የተሻለ አፈፃፀም ያላቸውን ት/ቤቶች የአሰራር ዘዴዎች መውሰድ የበለጠ አቅም እንደሚፈጥር ተገልፃል፡፡

ስልጠናው ጥቃትን ከመከላከል አንፃር በ11 ዱ ክፍለ ከተሞች የተሻለ አፈፃፀም ላሳዩ የክ/ከተማና ወረዳ ዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ባለሞያዎች፤ ሱፐር ቫይዘሮችና ርዕሳነ መምህራን በሶስት ዙር እንደሚሰጥ ከዳይሬክቶሬቱ ያገኘነው መረጃ ያሳያል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 14/5/2014 ዓ.ም

ማስታወቂያ!

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 10/5/2014 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ አቶ ዘላለም ሙላቱ ደሙ ለመላዉ የክርስትና ዕምነት ተከታዩች በሙሉ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ አቶ ዘላለም ሙላቱ በክርስትና ዕምነት ተከታዩች የሚከበረዉን የብርሃነ ጥምቀት በዓልን አስመልከተዉ ባስተላለፉት የእንኳን በሰላም አደረሳችሁ መልዕክታቸዉ እንደገለጹት በመከናወን ላይ ያሉ የትምህርት ልማት ስራዎች ውጤታማነታቸዉ ሊረጋገጥ የሚችለዉ ጤናዉ በተጠበቀ የትምህርት ማህበረሰብ በመሆኑ ጤናዉ የተስተካከለ የትምህርት ማህበረሰብ በመፍጠር ሂደት ውስጥ የትምህርት ባለድርሻ አኳላት በዓለ ጥምቀቱን በሚያከብሩበት ጊዜ በዓሉ በጋራ መሰባሰብ የሚከበር በመሆኑ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል በጤና ባለሙያዎች የሚመከሩ ጥንቃቄዎችን ያለምንም መዘናጋት በመተግበር ሊሆን ይገባዋል ብለዋል፡፡

የትምህርት ስራ በአንድ አካል ጥረት ብቻ የሚሳካ አለመሆኑን የገለጽት ሀላፊዉ ተወዳዳሪ የሆኑ ዜጎችን በመቅረጽ እና ለሀገር እድገት አስተዋጽዎ የሚያበረክቱ የሀገር መሰረቶችን በማፍራት ተግባር ውስጥ የትምህርት ተቋማቶቻችንን የልህቀት ማዕከል ለማድረግ ተግተን ልንሰራ ይገባል ብለዋል፡፡

ሀላፊዉ አክለዉም በዓሉም ሀገራችን ተገዳ በገባችበት የህልውና ዘመቻ ወቅት ላይ የሚከናወን በመሆኑ በጦርነቱ የተጎዱ አካላትን በመደገፍ ፣ በሆስፒታል የሚገኙ የመከላከያ ስራዊት አባላትን በመጠየቅ እና አቅመ ደካሞችን በመደገፍ በመተሳሰብ መንፈስ ልናከብረዉ ይገባል ብለዋል፡፡

በመጨረሻም ለመላዉ የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለአየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት በሰላም አደረሳችሁ በማለት በዓሉ የመተሳሰብ ፣ የሰላም ፣ የፍቅር እና የጤና እንዲሆን ተመኝተዋል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 10/5/2014 ዓ.ም

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የወሳኝ ኩነት ጽ/ቤት የተማሪዎች የልደት ካርድ ምዝገባ ማከናወን ጀመረ፡፡

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ  ወሳኝ ኩነት ምዝገባና መረጃ ቅ/ጽ/ቤት ከትምህርት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ባዘጋጀው ፕሮግራም “የተማሪ የልደት ምዝገባ ለተሻለ የትምህርት ጥራት” በሚል መሪ ቃል በጎሮ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት የከተማ፣የክ/ከተማና የወረዳ አመራሮቾን ፣ መምህራንና ተማሪዎችን  ያሳተፈ የተማሪዎች የልደት ካርድ ምዝገባ ንቅናቄ ማድረክ አካሂዳል፡፡

በእለቱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወሳኝ ኩነት ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር  ዶክተር  ታከለ ነጫና ፣የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳዊት ወልደየሱስ እና የወሳኝ ኩነት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ባጫ ጅረኛ በስፍራው ተገኝተዋል፡፡

በንቅናቄው ፕሮግራም ላይ የተገኙት ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚው የመክፈቻ ንግግር በማድረግ የልደት ምዝገባ ንቅናቄውን በይፋ አስጀምረዋል።

የለሚ ኩራ ወሳኝ ኩነት ሀላፊም በበኩላቸው የልደት ካርድን ከወሳኝ ኩነት ጽ/ቤት መውሰድ ያለውን ጠቀሜታ እና ሌሎች ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮች በተመለከተ አጭር ማብራሪያ መስጠታቸዉን ከክፍለ ከተማዉ ት/ጽ/ቤት እና ኮሚዩኒኬሽን ያገኘነዉ መረጃ ያሳያል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 9/5/2014 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ድጋፋ ሰጪ ዳይሬክቶሬቶች የ2014 ዓ.ም በጀት ዓመት የስድስት ወራት የስራ እቅድ አፈጻጸም ግምገማ ተደረገ፡፡

የዘርፉ መሪ እና የቢሮ ሀላፊ ጽፈት ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ሲሳይ እንዳለ በውይይቱ መክፈቻ እንደተናገሩት ሪፖርት የተሰሩ ጠንካራ ጎኖችን ብቻ የምናይበት ሳይሆን ያሉ ክፍተቶችንም  በጋራ በማየት ፡ እርስ በእርስ በመመካከርና በመግባባት  ወደተሻለ የስራ አፈጻጸም ለማምጣት የሚያስችለንም ጭምር መሆን አለበት ሲሉ አስገንዝበዋል፡፡

በግምገማው ላይ በየስራ ክፍሉ የተሰሩ ስራዎች ጥንካሬ የጋጠሙ ችግሮችና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን በዝርዝር ለውይይት ቀርቧል፡፡ ተሳታፊ አካላትም በቀረቡት ሪፖርቶች ላይ ውይይት አድርገዋል ፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!