ቀን 22/11/2014 ዓ.ም

የሬዲዮ ትምህርት ይዘት መረጣ ግምገማ መካሄድ ጀመረ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አሰተዳደር ትምህርት ቢሮ ኤፍ ኤም 94.7 የትምህርት ሬዲዮ ጣቢያ በኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ተዘጋጅቶ እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የተተረጎመውን ስርዓተ ትምህርት መሰረት በማድረግ ለአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች እገዛ የሚያደርግ የሬዲዮ ትምህርት ዝግጅት የይዘት መረጣ በአማርኛ እና በአፋን ኦሮሞ ቋንቋዎች ካከናወነ በሃላ ወደ ግምገማ ሂደት መግባቱን አሳውቋል፡፡ 

የአዲስ አበባ ከተማ አሰተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ትምህርት ቴክኖሎጂ ልማት እና ትግበራ ዳይሬክተር የሆኑት አቶ በለጠ ንጉሴ እንደታናገሩት በኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ተዘጋጅቶ እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የተተረጎመውን ስርዓተ ትምህርት መሰረት በማድረግ ለአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች እገዛ የሚያደርግ የሬዲዮ ትምህርት ዝግጅት የይዘት መረጣ በአማርኛ እና በአፋን ኦሮሞ ቋንቋዎች ሲካሄድ ቆይቶ መጠናቀቁን በመግለጽ ከዛሬ እለት ጀምሮ ወደ ግምገማ ምዕራፍ ገብቷል ብለዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አሰተዳደር ትምህርት ቢሮ ኤፍ ኤም 94.7 የትምህርት ሬዲዮ ጣቢያ ቡድን መሪ ወ/ሮ በላይነሽ የሻው በበኩላቸዉ የተከናወነው ይዘት መረጣ በአግባቡ ለመከናወኑ መገምገሙ እጅግ አስፈላጊ ሂደት መሆኑን በመጥቀስ ይዘት መረጣዉ ትክክለኛ ለመሆኑ፣ ተገቢ ይዘቶች በትክክል ስለመኖራቸዉ ፣ ሁሉም የትምህርት ምዕራፎች ስለመካተታቸዉ እና የይዘት መረጣዉ በቂ ስለመሆኑ ይፈተሻል ብለዋል፡፡ ግምገማዉ እደተጠናቀቀ በግምገማዉ የተገኙ ግብዓቶችን የማካተት ሰራ በቀጣይ ይከናወናልም ብለዋል፡፡  

በግምገማዉ ላይ በመሳተፍ ላይ የሚገኙት ከአስራአንዱም ክፍለ ከተማ አዲሱን ስርዓተ ትምህርት በማዘጋጀት ላይ የተሳተፉ መምህራን፣ የስርዓተ ትምህርት ትግበራ ባለሙያዎች ፣ የኤፌም 94.7 የትምህርት ሬዲዮ ጣቢያ የሬዲዮ ፕሮግራም አዘጋጆች እና ከኦሮሚያ ክልል የመጡ የሬዲዮ ትምህርት አዘጋጆች መሆኑን ያገኘነዉ መረጃ ያሳያል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 22/11/2014 ዓ.ም

የሬዲዮ ትምህርት ይዘት መረጣ ግምገማ መካሄድ ጀመረ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አሰተዳደር ትምህርት ቢሮ ኤፍ ኤም 94.7 የትምህርት ሬዲዮ ጣቢያ በኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ተዘጋጅቶ እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የተተረጎመውን ስርዓተ ትምህርት መሰረት በማድረግ ለአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች እገዛ የሚያደርግ የሬዲዮ ትምህርት ዝግጅት የይዘት መረጣ በአማርኛ እና በአፋን ኦሮሞ ቋንቋዎች ካከናወነ በሃላ ወደ ግምገማ ሂደት መግባቱን አሳውቋል፡፡ 

የአዲስ አበባ ከተማ አሰተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ትምህርት ቴክኖሎጂ ልማት እና ትግበራ ዳይሬክተር የሆኑት አቶ በለጠ ንጉሴ እንደታናገሩት በኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ተዘጋጅቶ እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የተተረጎመውን ስርዓተ ትምህርት መሰረት በማድረግ ለአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች እገዛ የሚያደርግ የሬዲዮ ትምህርት ዝግጅት የይዘት መረጣ በአማርኛ እና በአፋን ኦሮሞ ቋንቋዎች ሲካሄድ ቆይቶ መጠናቀቁን በመግለጽ ከዛሬ እለት ጀምሮ ወደ ግምገማ ምዕራፍ ገብቷል ብለዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አሰተዳደር ትምህርት ቢሮ ኤፍ ኤም 94.7 የትምህርት ሬዲዮ ጣቢያ ቡድን መሪ ወ/ሮ በላይነሽ የሻው በበኩላቸዉ የተከናወነው ይዘት መረጣ በአግባቡ ለመከናወኑ መገምገሙ እጅግ አስፈላጊ ሂደት መሆኑን በመጥቀስ ይዘት መረጣዉ ትክክለኛ ለመሆኑ፣ ተገቢ ይዘቶች በትክክል ስለመኖራቸዉ ፣ ሁሉም የትምህርት ምዕራፎች ስለመካተታቸዉ እና የይዘት መረጣዉ በቂ ስለመሆኑ ይፈተሻል ብለዋል፡፡ ግምገማዉ እደተጠናቀቀ በግምገማዉ የተገኙ ግብዓቶችን የማካተት ሰራ በቀጣይ ይከናወናልም ብለዋል፡፡  

በግምገማዉ ላይ በመሳተፍ ላይ የሚገኙት ከአስራአንዱም ክፍለ ከተማ አዲሱን ስርዓተ ትምህርት በማዘጋጀት ላይ የተሳተፉ መምህራን፣ የስርዓተ ትምህርት ትግበራ ባለሙያዎች ፣ የኤፌም 94.7 የትምህርት ሬዲዮ ጣቢያ የሬዲዮ ፕሮግራም አዘጋጆች እና ከኦሮሚያ ክልል የመጡ የሬዲዮ ትምህርት አዘጋጆች መሆኑን ያገኘነዉ መረጃ ያሳያል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 22/11/2014 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የለውጥና መልካም አስተዳደር ቡድን ከሀምሌ 18/2014 ዓ.ም ጀምሮ ሲያካሂድ የቆየውን የ2014 በጀት ዓመት የትምህርት ተቋማት የቢ ኤስ ሲ ስኮር ካርድ እቅድ አፈጻጸም ምዘና ማጠናቀቁን አስታወቀ።

ምዘናው በሁሉም የመንግስት አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች፣በክፍለ ከተማና ወረዳ ትምህርት ጽህፈት ቤቶች እንዲሁም በማዕከል ደረጃ ተካሂዶ በዛሬው እለት መጠናቀቁን የቢሮው የለውጥና መልካም አስተዳደር ቡድን መሪ ወይዘሮ እጸገነት አብዱ ገልጸው በሂደቱም 324 መዛኞችና 22 አስተባባሪዎች መሳተፋቸውን አስታውቀዋል።

ቡድን መሪዋ አክለውም ምዘናው በስኬት እንዲጠናቀቅ ከመመዘኛ መስፈርት ዝግጅት ጀምሮ ለመዛኞችና አስተባባሪዎች ኦረንቴሽን ተሰጥቶ ወደ ምዘና መገባቱን ጠቁመው የላቀ አፈጻጸም ያስመዘገቡ ተቋማት የምዘና ውጤቱን መሰረት በማድረግ እውቅና እንደሚሰጣቸው አስገንዝበዋል።

ምዘናው ያለምንም እንከን እንዲጠናቀቅ  ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ለተወጡ መዛኞችና አስተባባሪዎችን ጨምሮ ለተመዛኝ ተቋማት ላቅ ያለ ምስጋና እንደሚገባቸው ቡድን መሪዋ አስረድተዋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 22/11/2014 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአሜሪካ ኦሪገን በተካሄደ 18ኛው ዓለም ዐቀፍ የአትሌቲክስ ሻምፕዮና ላይ ሜዳሊያ ላመጡ አትሌቶች የመኖሪያ ቤት መሥሪያ ቦታ እና የገንዘብ ሽልማት አበረከተ።

ሽልማቱ በከተማው አስተዳደር ካቢኔ የተወሰነ ሲሆን

* አትሌት ለተሰንበት ግደይ 500 ካሬ ሜትር መሬት

* አትሌት ጎተይቶም ገ/ስላሴ 500 ካሬ ሜትር መሬት

* አትሌት ታምራት ቶላ 500 ካሬ ሜትር መሬት

* አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ 500 ካሬ ሜትር

* አትሌት ለሜቻ ግርማ 350 ካሬ ሜትር መሬት

* አትሌት ሞስነት ገረመው 350 ካሬ ሜትር መሬት

* አትሌት ወርቅውሃ ጌታቸው 350 ካሬ ሜትር መሬት

* አትሌት መቅደስ አበበ 250 ካሬ ሜትር መሬት

* አትሌት ዳዊት ስዩም 250 ካሬ ሜትር መሬት

ለአጠቃላይ የልኡኩ አባላት ደግሞ የ10 ሚሊዬን ብር ሽልማት ተበርክቷል::

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 21/11/2014 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት እና ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ ስራተኞች ለአትሌቶች የምስጋና መርኃ ግብር አካሄዱ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት እና ዲዛይንና ግንባታ ቢሮዎች ስራተኞች ጀግኖች አትሌቶች በ18ኛው አትሌቲክስ ሻምፒዮና ውድድር ላስመዘገቡት ድል የምስጋና መርኃ ግብር አካሄዱ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፎ ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ አትሌቶቻችን ባስመዘገቡት አንፀባራቂ ድል ዙሪያ ያስተላለፉት መልዕክት ባለፉት ጥቂት ዓመታት እንደ ሀገር ፈተና ያጋጠመን ቢሆንም ለችግሮቻችን ስንበረከክ የኢትዮጵያን አኩሪ የድል ታሪክ መጻፍ የቻልን ትውልድ በመሆናችን ደስታ ይሰማናል ፤ በአንድነት የማሽነፍ እሴትንም አጠናክረን ልናስቀጥል ይገባል ብለዋል፡፡ አክለውም ምስጋናን ባህል በማድረግ የተሻለ የሰራን በማመስገን ለላቀ አፈጻጸም መትጋት ውጤታማ የሚያደርግ በመሆኑ በመመሰጋገን እና በጽናት በመጓዝ የበለጸገች ሀገርን ለመፍጠር በትኩረት መስራት ከሁሉም ይጠበቃል ብለዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ ኃላፊ ክብርት ኢ/ር አያልነሽ ሐብተማርያም ይህ ታሪክ የኢትዮጵያን ጥንካሬ ፤ የኢትዮጵያን ሀያልነት ፤ የኢትዮጵያን አልበገር ባይነት ለማየት ለማይፈልጉት ሐገራት ጥሩ ማሣያ ሲሆን በተያያዥነትም ይህ ታሪካዊ ኩነት ደግሞ በሀገረ አሜሪካ  ምድር ላይ በደማቅ ቀለም  መፃፉ ከታሪክም፤ ከድልም በላይ ልዩና ጣፋጭ ያደርገዋል ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ በብዙ ፈተናና ውጣ ውረድ ብትፈተንም በፅናት ተቋቁማ ያገኘችውን ድል በማስመልከት ነው ለጀግኖች አትሌቶች የምስጋና መርኃ ግብሩ የተካሄደው፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 21/11/2014 ዓ.ም

በ18ኛው ዓለም አትሌትክስ ሻምፒዮና አኩሪ ድል ላስመዘገበው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን የጎዳና ላይ አቀባበል  በፎቶ

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 21/11/2014 ዓ.ም

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 20/11/2014 ዓ.ም

ጀግኖቹ እናት ምድር ኢትዮጵያ ገቡ፡፡

በአሜሪካ ኦሪገን በተካሄደው 18ኛው የዓለም አትሌትክስ ሻምፒዮና አኩሪ ድል ያስመዘገበው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን አዲስ አበባ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል፡፡

የአትሌቲክስ የልዑካን ቡድኑ አባላት  ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡

በአቀባበል ሥነ ሥርዓቱ ላይ የባህልና ስፖርት ሚኒስትሩ  ቀጀላ መርዳሳ  ፣የባህልና ስፖርት ሚ/ር የስፖርት ዘርፍ ሚ/ር ዴኤታ አምባሳደር መስፍን ቸርነት፣የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ፣የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ  እና ሌሎች   ተገኝተዋል።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ “ዛሬም እንደ ትናንቱ፥ ፈተናዎችን በድል ተሻግረን፣ እጃችንን ለምስጋና እንዘረጋለን” በሚል መሪ ሀሳብ ባስተላለፉት መልዕክት፥ “የውስጥ ፈተናውንና የውጪ ጫናውን ተቋቁመው በዓለም የስፖርት መድረክ ላይ በድል ላይ ድል የሚቀዳጁት፥  በስፖርት አደባባይ የእናት ሀገራቸውን ሰንደቅ ከፍ አድርገው እያውለበለቡ፣ ድል ባደረጉበት ሜዳ ላይ እጆቻቸውን ወደ ሰማይ ዘርግተው ፈጣሪያቸውን የሚያመስግኑ ኢትዮጵያውያን” መሆናቸውን አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን በኦሪገን ያስመዘገበው አኩሪ ድል ከተባበርን በድል አድራጊነታችን እንደምንቀጥልና መሰናክሎችን ሁሉ እንደምንሻገራቸው ያሳየ መሆኑን የገለጹት ደግሞ  በጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት በሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ዶክተር ቢቂላ ሁሪሳ ናቸው።

አትሌቶቻችን በዓለም አደባባይ በፈፀሙት ጀግንነት የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ከፍ እንዲልና ክብሯ እንዲወሳ አድርገዋል ሲሉም ነው የገለጹት።

በነገው ዕለት መንግሥት ለአትሌቲክስ ቡድን የጀግና አቀባበል እንደሚያደርግለት የገለጹት ዶክተር ቢቂላ፥  ኢትዮጵያ ታመስግን የሚል መርሐ ግብርም እንደሚከናወን ጠቅሰዋል።

በነገው ዕለት ሕዝቡ ለጅግኖች አትሌቶቹና ለሌሎች የልዑኩ አባላት አድናቆቱን በመግለጽ የጀግና አቀባበል የሚያደርግላቸው ሲሆን፥ የአትሌቲክስ ቡድኑ ካረፈበት ስካይላይት ሆቴል ከጠዋቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ በአጀብ በአዲስ አበባ ከተማ ዋና ዋና ጎዳናዎች በደማቅ ሁኔታ እንደሚጓዝ ታውቋል።

200 ሀገራት በተሳተፉበት 18ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ የተካፈለችው ኢትዮጵያ 4 የወርቅ ፣ 4 ብር እና 2 የነሐስ በድምሩ 10 ሜዳሊያዎችን በማግኘት ውድድሩን ከአፍሪካ በአንደኛነት ከዓለም ከአሜሪካ ቀጥላ በ2ኛ ደረጃነት ማጠናቀቁ ይታወሳል፡፡

ነገ  የአትሌቲክስ ቡድኑ ካረፈበት ስካይላይት ሆቴል ጀምሮ  በአጀብ በአዲስ አበባ ከተማ ዋና ዋና ጎዳናዎች ስለሚጓዝ የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑም የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 20/11/2014 ዓ.ም

ተማሪዎች ውጤታችሁን በየትምህርት ቤታችሁ ማየት እና መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2014 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ የሆነ ሲሆን ለፈተና ከተቀመጡ ተማሪዎች መካከል 63.9 ፐርሰንት ተማሪዎች 50 እና በላይ ውጤት ማስመዝገብ ችለዋል፡፡ ይህም ካለፉት አመታት ከተመዘገቡት ከተማ አቀፍ የ8ኛ ክፍል ውጤቶች አንጻር ሲታይ ከፍተኛ ውጤት ሆናል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ 85..5% ተማሪዎች ወደቀጣይ ክፍል ለመዛወር ችለዋል፡፡

ተማሪዎችም ውጤታችሁን በተገለጸው ሊንክ እንድታዩ ይፋ የተደረገ ቢሆንም በተፈጠረው የኔቶርክ መጨናነቅ ምክንያት ውጤታችሁን ለማየት ያልቻላችሁ ተማሪዎች በየትምህርት ቤታችሁ ማየት እና መውሰድ እንደምትችሉ እናሳውቃለን፡፡  

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 19/11/2014 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የለውጥና መልካም አስተዳደር ቡድን የ2014 በጀት አመት የትምህርት ተቋማት የቢ ኤስ ሲ ስኮር ካርድ እቅድ አፈጻጸም ምዘና በመካሄድ ላይ እንደሚገኝ አስታወቀ ።

ምዘናው ከትላንት ጀምሮ በሁሉም የመንግስት አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች፣ በክፍለ ከተማና ወረዳ ትምህርት ጽህፈት ቤቶች እንዲሁም በማዕከል ደረጃ በመካሄድ ላይ እንደሚገኝ የቢሮው የለውጥና መልካም አስተዳደር ቡድን መሪ ወይዘሮ እጸገነት አብዱ ገልጸው በሂደቱም 324 መዛኞችና 22 አስተባባሪዎች ተሳታፊ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

ቡድን መሪዋ አክለውም ምዘናው በስኬት እንዲጠናቀቅ ከመመዘኛ መስፈርት ዝግጅት ጀምሮ ለመዛኞችና አስተባባሪዎች ኦረንቴሽን ተሰጥቶ ወደ ምዘና መገባቱን ጠቁመው ምዘናው እስከ ሀምሌ 22/2014 ዓ.ም ድረስ እንደሚካሄድና የላቀ አፈጻጸም ያስመዘገቡ ተቋማት የምዘና ውጤቱን መሰረት በማድረግ እውቅና እንደሚሰጣቸው አስረድተዋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!