ቀን 22/4/2014 ዓ.ም

የኢንተርኔት ግንኙነት የሌላቸው ትምህርት ቤቶችን ሊጠቅም የሚችል ቴክኖሎጂ

ዲያስፖራው የኢንተርኔት ግንኙነት በሌለበት ቦታ የዲጂታል ትምህርት መስጠት የሚያስችል ቴክኖሎጂ ለሙከራ ይዘው መጡ፡፡

ከ40 አመት በላይ አሜሪካን ሀገር የኖሩት አቶ ሚዴቅሳ በየነ የኢንተርኔት ግንኙነት በሌለበት ቦታ የዲጂታል ትምህርት መስጠት የሚያስችል መሳሪያ ለሙከራ ለሀገራቸው ይዘው መጥተዋል።

አቶ ሚደቅሳ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ወደ ሀገር ቤት መመለስ ጥሪን ተቀብለው ወደ ሀገራቸው የመጡ ትውልደ ኢትዮጵያዊ ናቸው።

በዚህም መሰረት ወደ ሀገር ሲመጡ የኢንተርኔት ግንኙነት የሌላቸው ትምህርት ቤቶችን ሊጠቅም የሚችል ቴክኖሎጂ ይዘው እንደመጡ ተናግረዋል።

ቴክኖሎጂው በሶላር ሃይል የሚሰራ፣ የራሱ ዋይፋይ ያለውና ተንቀሳቃሽ 2 ቴራባይት ሰርቨር የያዘ ሲሆን ከኮምፒውተርና ከሞባይል ጋር በማገናኘት የመማሪያ መሳሪያዎችን ማግኘት የሚቻልበት ነው።

ቴክኖሎጂው የተለያዩ የትምህርት አይነቶች የያዙ መፅሃፍት፣ መርጃ መፅሃፍት፣ ሌክቸሮችና ቪዲዮዎች፣ ጥናታዊ ፅሁፎች፣ ንግግሮች፣ መዝናኛዎች እና በሺዎች የሚቆጠሩ ሌሎችንም ማስረጃዎች የሚይዝ ነው።

ከ60 ሺ በላይ መፀሃፍትን የያዘው ስርዓቱ መፅሃፍቶቹን በማንኛውም ጊዜ በነፃ ማውረድም ያስችላል።

በአሁን ሰዓት መሳሪያውን በሀገር ውስጥ ለመጠቀም እንዲቻል የትምህርት ሚኒስቴር የአይሲቲ ባለሙያዎች እንዲገመግሙት እየተደረገ ነው።

ባለሙያዎቹ ሲስተሙ ላይ የሀገር ውስጥ የትምህርት አይነቶችን በመጫን ሀገርኛ ይዘት እንዲኖረው የማድረግ ስራዎችን እንደሚሰሩም ተገልጿል።በቀጣይ የዚህን ቴክኖሎጂ ውጤታማነት ተገምግሞ ቀጣይ ስራዎች ይሰራሉ ተብሏል።

ሌሎች ትውልደ ኢትዮጵያውያንም ወደ ሀገር ሲመጡ የትምህርት ስርዓቱን ሊያግዝ የሚችል ድጋፍ እንዲያደርጉ የትምህርት ሚኒስቴር ጠይቋል።

አካባቢያችንን #እንጠብቅ

ወደ ግንባር #እንዝመት

መከላከያን #እንደግፍ

ከደጀን እስከ ግንባር ከኢትዮጵያ ሰራዊት ጎን ነን!

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 20/4/2014 ዓ.ም

በአንድ ማዕከል ለዲያስፖራዎች አገልግሎት መስጠት ተጀመረ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤና ሌሎች ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት አዲስ የዳያስፖራ ማዕከል ዛሬ በይፋ ስራ የጀመረ ሲሆን ማዕከሉ የማህበራዊ ዘርፍ ፣ የኢንቨስትመንት ፣ የኢሚግሬሽንና ሌሎችም አገልግሎቶች በአንድ ማዕከል የሚሰጥበት ነዉ፡፡

አገልግሎቱም የበአል ቀናትን ጨምሮ እስከ ምሽት 12 ሰዓት ድረስ የሚሰጥ ሲሆን ማዕከሉ በኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ጥሪ መሰረት ወደ አገርቤት ለመጡ ዳያስፖራዎች የተለያዩ የመረጃ አገልግሎቶችን የሚሰጥ ነዉ፡፡

በዚህ ማዕከል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የማህበራዊ ዘርፍ ተቋማትም እንኳን ወደ እናት ሀገራችሁ ኢትዮጵያ በሰላም መጣችሁ! እያሉ የዲያስፖራ ማህበረሰቡ አካላት በከተማ አስተዳደሩ በሚከናወኑ የማህበራዊ ዘርፉ ስራዎች ላይ የተደራጀ መረጃ በማግኘት ለማህበራዊ ዘርፉ መጎልበት የድርሻቸዉን እንዲወጡ የመረጃ አገልግሎቱን መስጠት ጀምረዋል፡፡

አካባቢያችንን #እንጠብቅ

ወደ ግንባር #እንዝመት

መከላከያን #እንደግፍ

ከደጀን እስከ ግንባር ከኢትዮጵያ ሰራዊት ጎን ነን!

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 20/4/2014 ዓ.ም

የሰሞኑ ጉንፋን መሰል ህመምና መፍትሄዎቹ!

የሰሞኑ ጉንፋን ለየት የሚያረገው ከፍተኛ ትኩሳት እና ጠንከር ያለ ሳል ያለዉ ስሆን በተጨማሪም እነዚህ ምልክቶች ይታዩበታል፡፡

  • ብርድ ብርድ ማለት
  • የመገጣጠሚያ ህመም
  •  የጀርባ ህመም
  •  የጡንቻ ህመም
  • ምግብ ፍላጎት መቀነስ
  • ኃይለኛ ራስ ምታት
  •  ፍዝዝ ማለት
  1. ምክንያቱ ምን ሊሆን ይችላል?
  • ጉንፋን ዋና መንስኤዎቹ በትንፋሽ በሳል እና በማስነጠስ የሚተላለፉ ቫይረሶች ናቸው::
  • መፍትሄዉ?
  • ሁሌም የአፍ እና አፍንጫን መሸፈን
  • የእጅ እና አካል ንክኪን መቀነስ
  • ሰዉ የሚሰበብበት ቦታ አለመገኘት
  • ስያስሉ እና ሲያስነጥሱ አፍ እና አፍንጫዎን በክንድዎ/በጨርቅ መሸፈን
  • መንግስት በነፃ ያቀረበውን የኮሮና ክትባት መውሰድ
  • የቤት ዉስጥ ሕክምናው ለልጆች እና ለህፃናት
  • ለብ ያለ ዉሃ ዉስጥ ትንሽ ጨው አርጎ አፍንጫቸው ቀዳዳ ዉስጥ 2 ጠብታ ማድረግ በመቀጠል የአፍንጫ ቀዳዳዎችን በመምጠጫ ማጽዳት
  • ትኩሳትን የሚቀንስ መድሃኒት መጠቀም
  • ትኩስ ትኩስ ነገሮችን ማጠጣት
  • ተጨማሪ ምግቦችን በደንብ መመገብ
  • የሕፃኑን ክፍል በደንብ ማፅዳት ማናፈስ
  • ቤቱን በውሀ እንፋሎት ማጠን
  • ንፍጥ እና ትኩሳት በጣም አስፈላጊ ፈሳሾችን እና ንጥረ ነገሮችን ይዘው ስለሚወጡ ተጨማሪ ፈሳሽ ነገሮችን ማግኘት ይኖርባቸዋል ::
  • የቤት ዉስጥ ሕክምና ለታዳጊ ህፃናት እና ለአዋቂዎች
  • ከላይ ከተዘረዘሩት በተጨማሪ ራስን በአንድ ክፍል ማግለል
  • ትኩስ ፈሳሽ ነገሮችን ደጋግሞ መውሰድ
  • ነጭ ሽንኩርት ማር እና ዝንጅብል መጠቀም
  • በቂ እረፍት ማድረግ
  • የትኩሳት እና ራስ ምታት ማስታገሻ መውሰድ

እነዚህን መፍትሄዎ እያረጋችሁ ምንም ለውጥ ከሌለው እና ሳሉ የመባስ ትኩሳቱ የመጨመር ባህሪ ካለው ወይም ትንፋሽ የማጠር ምልክት በህፃንም ሆነ በአዋቂ ላይ ካለ በአፋጣኝ ሆስፒታል መሄድ ያስፈልጋል፡፡

ምንጭ ፡- በዶ/ር ፋሲል መንበረ በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ ረዳት ፕሮፌሰር እና የሕጻናት ስፔሻሊስት ሐኪም

አካባቢያችንን #እንጠብቅ

ወደ ግንባር #እንዝመት

መከላከያን #እንደግፍ

ከደጀን እስከ ግንባር ከኢትዮጵያ ሰራዊት ጎን ነን!

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 20/4/2014 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ ቡድን በቅርቡ በ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለተመደቡ የአይ ሲ ቲ ባለሙያዎች ስልጠና ሰጠ።

ስልጠናው በዋናነት በስኩል ኔት መሰረት ልማት አጠቃቀም እና ተዛማጅ ጉዳዮችን በተመለከተ የተዘጋጀ ሲሆን ስልጠናውም በስራ ክፍሉ ባለሙያዎች በአቶ ታዬ ወልደኪዳን እና በአቶ ሚካኤል መስፍን ነው የተሰጠው።

በስልጠናው መክፈቻ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳኘው ገብሩ እንዳስታወቁት ስልጠናው በቅርቡ ቢሮው ባወጣው ማስታወቂያ ተወዳድረው በየትምህርት ቤቱ የተመደቡ ባለሙያዎች ሙያዊ ክህሎታቸውን ማሻሻል እንዲችሉ ታስቦ መዘጋጀቱን ገልጸው የስልጠናው ተሳታፊዎችም በትምህርት ቤቶች ያሉ የአይ ሲ ቲ መሰረተ ልማቶች ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጡ የተጣለባቸውን ኃላፊነት በአግባቡ ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የስልጠናው ተሳታፊዎች በቀረቡ የስልጠና ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የተለያዩ አስተያየቶችን እና ጥያቄዎችን ያቀረቡ ሲሆን በዋናነትም የስራ ድርሻቸው በአስቸኳይ ለትምህርት ቤቶች ቢላክ የሚልና አንዳንድ ትምህርት ቤቶች ተገቢውን ድጋፍ አለማድረጋቸውን አንስተው በቢሮው የአጠቃላይ ትምህርት ቴክኖሎጂ ልማትና ትግበራ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በሆኑት በአቶ በለጠ ንጉሴ እና በኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ ቡድን መሪው በአቶ ደረጀ ዳኜ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ተሰጥቷል።

አካባቢያችንን #እንጠብቅ

ወደ ግንባር #እንዝመት

መከላከያን #እንደግፍ

ከደጀን እስከ ግንባር ከኢትዮጵያ ሰራዊት ጎን ነን!

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 19/4/2014 ዓ.ም

የዋንጫ ሽልማት ሳምንት በአብዮት የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት፡፡

በአራዳ ክፍለ ከተማ በአብዮት የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት የዋንጫ ሽልማት ሳምንት በመከበር ላይ ነዉ፡፡ የሽልማቱ ዋና አላማ በተማሪዋች መካከል የውድድር መንፈስን በመፍጠር ፣ የመረዳዳት ባህልን የሚያጎለብቱበት እና ለተሻለ ውጤት የሚተጉበት ሌላኛዉ መንገድ አድርጎ እየተጠቀመበት እና የተሻለ ለውጥ እንዲመዘገብ ያገዘ መሆኑን ትምህርት ቤቱ ገልጻል።

ትምህርት ቤቱ የሚያከብረው የዋንጫ ሳምንት በወርሀዊ ፈተና ሁሉም ተወዳዳሪ የሚሆንበት እድል ያለው ሲሆን ጓደኞቻቸዉን በማስጠናት እና በወርሃዊ ፈተና 10 ከ10 የደፈኑ ተማሪዎችን ብዛት በየክፍሉ በመቁጠር የላቀ አፈጻጸም ያለዉ ክፍል አሽናፊ የሚሆንበት ነዉ፡፡

በዚህ የዋንጫ ሽልማት ሳምንትም ጓደኞቻቸውን በማስጠናት የላቀ ውጤት ያስመዘገቡ ክፍሎች የ1A ፣ የ2B እና የ3A  ክፍል ተማሪዎች ሲሆኑ ዋንጫዉን ከወተመህ እና ከት/ቤቱ ርዕሰ መምህር በመረከብ በቀጣይም ጓደኞቻቸውን በመረዳት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ቃል ገብተዋል።

ለዚህ የዋንጫ ሽልማት ሳምንት መሳካትም ከፍተኛ ሚና ለተጫወቱ መምህራን ትምህርት ቤቱ ምስጋና አቅርባል።

አካባቢያችንን #እንጠብቅ

ወደ ግንባር #እንዝመት

መከላከያን #እንደግፍ

ከደጀን እስከ ግንባር ከኢትዮጵያ ሰራዊት ጎን ነን!

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 15/4/2014 ዓ.ም

ሀገራዊ የተማሪዎች የጫማና ቦርሳ ፕሮጀክት ትግበራ ይፋ ተደረገ፡፡

ሀገራዊ የተማሪዎች የጫማና ቦርሳ ፕሮጀክት ትግበራ ይፋ መደረጉን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር  አቶ መላኩ አለበል አስታወቁ።

ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት ፅሁፍ፥ ፕሮጀክቱ በትምህርት ገበታ ላይ የሚገኙ 30 ሚሊየን ተማሪዎችን ታሳቢ ያደረገ  መሆኑን ገልፀዋል።

ፕሮጀክቱ የገቢ ምርትን በመተካት፣ የስራ እድል በመፍጠር እና ጥራት ያለው ምርትን ለገበያ በማቅረብ ኢኮኖሚውን ያነቃቃል ነው ያሉት።

አካባቢያችንን #እንጠብቅ

ወደ ግንባር #እንዝመት

መከላከያን #እንደግፍ

ከደጀን እስከ ግንባር ከኢትዮጵያ ሰራዊት ጎን ነን!

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 15/4/2014 ዓ.ም

የልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት ባካሄደዉ ክትትልና ድጋፍ ላይ ውይይት አደረገ፡፡

በ19ኙ ግቦች ዙሪያ ለሁሉም የመንግስት የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች እና ለወረዳ ትምህርት ጽ/ቤቶች ፣ በ8ኛ እና በ12ኛ ክፍል ውጤት ማሻሻያ ልዩ ዕቅድ እና በተከናወኑ ተግባራት፣ በልዩ ፍላጎት ትምህርት፣ በውስጥና በውጪ በልምድ ልውውጦች፣ በመልካም አስተዳደር፣ ከኮቪድ-19 ጋር ተያይዞ በሚደረጉ ጥንቃቄዎች፣ በተማሪዎች ጥያቄና መልስ ውድድር፣ በምገባ ስርዓት እና በሌሎችም ዋና ዋና ነጥቦች ላይ ትኩረት ያደረገ ክትትልና ድጋፍ መደረጉ በውይይቱ ተገልጻል፡፡

በክትትልና ድጋፉ የተገኙ ግኝቶች፣ የታዩ ጠንካራ ጎኖች እንዲሁም መሻሻል የሚገባቸው ጉዳዮችን በተመለከተ ክትትልና ድጋፍ ያደረጉ ባለሙያዎች ሪፖርት አቅርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡

የክፍለ ከተማዉ ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሪት እጅጋየሁ አድማሱ በቀጣይ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮችን በመለየት ትኩረት ተደርጎ መሰራት እንዳለበት ፣ በክ/ከተማ ደረጃ መፈታት የሚገባቸው የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች፣ የምገባ ስርዓቱ ውጤታማ ሆኖ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን ፣ የቅዳሜ ማጠናከሪያ ትምህርት ለ8ኛ እና12ኛ ከፍል ተማሪዎች እየተሠጠ መሆኑን ፣ ከኮቪድ ጋር ተያይዞ ከጤና ቢሮ በወረደው አቅጣጫ መሠረት ሁሉም መምህራን፣ ር/መምህራን፣ የአስ/ሠራተኞች እና ከ18 ዓመት በላይ የሆኑ ተማሪዎች ክትባት መከተባቸውን እንዲሁም ለወረዳ ትምህርት ጽ/ቤቶች ተከታታይነት ያለው ክትትልና ድጋፍ ማድረግ በዋናነት ትኩረት ተደርጎ የሚሠራባቸው ስራዎች ይሆናሉ ብለዋል፡፡

አካባቢያችንን #እንጠብቅ

ወደ ግንባር #እንዝመት

መከላከያን #እንደግፍ

ከደጀን እስከ ግንባር ከኢትዮጵያ ሰራዊት ጎን ነን!

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 15/4/2014 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ዙሪያ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር የሚያደርገውን ውይይት በመቀጠል በዛሬው እለት ከጤና አመራሮች እና ባለሙያዎች ጋር ተወያይቱዋል።

በውይይቱ መክፈቻ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዮሀንስ ጫላ ባስተላለፉት መልዕክት ሀገራችን ኢትዮጵያ ተገዳ የገባችበትን የህግ ማስከበርም ሆነ የህልውና ዘመቻ በድል እንድታጠናቀቅ የጤና ሴክተሩ ከደጀንነት ጀምሮ ግንባር ድረስ እስከመዝመት የደረሰ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸው በጦርነቱ ምክንያት የወደሙ የጤና ተቋማት ዳግም አገልግሎት እንዲጀምሩ 75 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ መደረጉን አስታውቀዋል።

በመርሀ ግብሩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ተወካይ አቶ ዘላለም ሙላቱ በበኩላቸው ኢትዮጵያ ተገዳ ከገባችበት ጦርነት በፍጥነት ተላቃ ወደ መደበኛው የልማትና ብልጽግና ጎዳና እንድትመለስ የጤናው ሴክተር አስተዋጽኦ ከፍተኛ በመሆኑ ውይይቱን ማካሄድ ማስፈለጉን ገልጸው ከአሸባሪው ቡድን ነጻ በወጡ አከባቢዎች የወደሙ ተቋማትን ወደስራ ለማስገባት የጤናው ሴክተር ያበረከተው አስተዋጾ ከፍተኛ መሆኑን እና በቀጣይም ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

የውይይቱ ተሳታፊዎችም ሀገሪቱ ተገዳ የገባችበትን ጦርነት በድል እንድታጠናቅቅ ህይወታቸውን ከመገበር ጀምሮ የተለያዩ መስዋእትነቶችን ለከፈሉ የመከላከያ ሰራዊት አባላት እና መላው የጸጥታ መዋቅሮች ምስጋና አቅርበው በጦርነቱ የወደሙ የጤና ተቋማትን ዳግም ስራ ለማስጀመር በሚደረገው እንቅስቃሴ ሙያዊ ድጋፍ ከማድረግ ጀምሮ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

አካባቢያችንን #እንጠብቅ

ወደ ግንባር #እንዝመት

መከላከያን #እንደግፍ

ከደጀን እስከ ግንባር ከኢትዮጵያ ሰራዊት ጎን ነን!

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 14/4/2014 ዓ.ም

የንባብ ዐውደ ርዕይ በዳግማዊ ሚኒሊክ መሰናዶ ትምህርት ቤት ተከፈተ፡፡

የአራዳ ክፍለ ከተማ ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ጽ/ቤት የቤተ-መፅሀፍት አገልግሎት ቡድን ባሰናዳው የንባብ ዐውደ ርዕይ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑት ረዳት ፕሮፌሰር ደረጄ ገብሬ፣ የተለያዩ መምህራንና የዳግማዊ ሚኒሊክ መሰናዶ ት/ቤት ተማሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

በንባብ የተሟላ ስብዕናው ያለው ትውልድ ለሀገር እድገት መሰረት ነው ያሉት ረዳት ፕሮፌሰር ደረጄ ትውልዱ የንባብ ባህሉን ያሳድግ ዘንድ በት/ቤቶች ግንዛቤ የማስፋት ስራ መሰራቱ ይበል የሚያሰኝ ነውና ሊቀጥል ይገባል ብለው የንባብ ልምዳቸውን ለተማሪዎች አካፍለዋል፡፡

የኪነ-ጥበብ ሀብቶች ልማት፣ የመድረክና ሁነት ዝግጅት ቡድን መሪ አቶ ዳዊት ግርማ በሀገራችን ማንኛውንም እድገት ለማምጣትና ሀገር ለማሻገር አንባቢ ትውልድ መፈጠር አለበት ብለው የእውቀት ምንጭ በሆኑት ትምህርት ቤቶች ላይ የንባብ ባህል ለማሳደግ ታስቦ በተዘጋጀው ዐውደ ርዕይ በክፍለ ከተማው ለሚገኘው መስከረም አንደኛ ደረጃ ት/ቤት የ52 መፅሀፍት ድጋፍ ይበረከታል ሲሉ ገልፀዋል፡፡

በመጨረሻም የዝግጅቱ ተሳታፊ ተማሪዎች በማንበብ የተለያዩ እውቀቶችና የህይወት ልምዶችን ማግኘት ስለምንችል የንባብ ባህላችንን ልናሳድግ ይገባል ብለዋል፡፡

አካባቢያችንን #እንጠብቅ

ወደ ግንባር #እንዝመት

መከላከያን #እንደግፍ

ከደጀን እስከ ግንባር ከኢትዮጵያ ሰራዊት ጎን ነን!

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 14/4/2014 ዓ.ም

በ8ኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል ጥያቄና መልስ ውድድር ተካሄደ፡፡

የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ትምህርት ፅፈት ቤት የአጠቃላይ ትምህርት ስርዓተ ትምህርት ትግበራና ክትትል ቡድን በክፍለ ከተማ ደረጃ በ8ኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል ጥያቄና መልስ ውድድር አካሄደ::

በጥያቄና መልስ ውድድሩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቂርቆስ ክፍለ ከተማ የስርዓተ ትምህርት ትግበራና ክትትል ቡድን መሪ አቶ ዘመቻ ዮሐንስ እንዳሉት የ2014 ዓ.ም የአንድ ገፅ እቅድ ላይ የተቀመጠዉን የተማሪዎች ውጤትን ማሻሻል ዋና አላማው ማድረጉን አውስተው በተማሪዎች መካከል የፉክክር ስሜት በመፍጠር ውጤታቸውን ማሻሻልና በስነ-ምግባር የታነፀ ትውልድ ለማፍራት እንደሚያግዝ ተናግረዋል ::

በክፍለ ከተማው ካሉ 42 አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 12ቱ ለዚህ የአሽናፊዎች አሽናፊ ውድድር የቀረቡ ሲሆን  በአማርኛ ስርዓተ የሰኒ ሳይድ ትምህርት ቤት ተማሪ የሆነችው ቅድስት አባይነህ እና በአፋን ኦሮሞ ስርዓተ ትምህርት የወርሃ የካቲት ትምህርት ቤት ተማሪ የሆነችው ወርቂቱ ሞላ አንደኛ በመሆን አጠናቀዋል፡፡

የጥያቄና መልስ ውድድሩም በሁሉም የትምህርት አይነቶች ላይ ያተኮረ መሆኑን ያገኘነው መረጃ ያሳያል::

አካባቢያችንን #እንጠብቅ

ወደ ግንባር #እንዝመት

መከላከያን #እንደግፍ

ከደጀን እስከ ግንባር ከኢትዮጵያ ሰራዊት ጎን ነን!

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!