ቀን 19 /2/ 2014 ዓ.ም

የመምህርነት ሙያ ቅጥር ማስታወቂያ

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 19 /2/ 2014 ዓ.ም

ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 በሚገኘው ሀና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች በምግብ መመረዝ ምክንያት ጉዳት እንደደረሰባቸው የሚወራው ወሬ ሀሰት መሆኑ ተገለጸ።

ጉዳዩን አስመልክቶ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ዘላለም ሙላቱ ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምገባ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬከተር አንቺነሽ ተስፋዬ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዶክተር ሙሉጌታ እንዳለ መግለጫ ሰጥተዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ዘላለም ሙላቱ እንዳስታወቁት በትምህርት ቤቱ ለግዜው ባልታወቀ ምክንያት ሁለት ተማሪዎች አደጋ እንዳጋጠማቸውና እነዚህን ተማሪዎች ያዩ የተወሰኑ ልጆች በድንጋጤ ራሳቸውን በመሳታቸው ወደ ህክምና ማዕከል መወሰዳቸውን ገልጸው ተማሪዎቹ በተደረገላቸው ምርመራ ምንም አይነት ከምግብ መመረዝ ጋር የተገናኘ ችግር እንዳላጋጠማቸው በመረጋገጡ ወደ ቤታቸው እንዲሄዱ መደረጉን አስረድተዋል።

ኃላፊው አክለውም ተማሪዎቹን ወደ ህክምና ማዕከላት ለመውሰድ አምቡላንሶች ወትምህርት ቤቱ ቅጥር ግቢ ሱገቡ በአከባቢው የተመለከቱ አካላት በፈጠሩት ግርግር ወላጆች ተደናግጠው ወደ ትምህርት ቤቱ መምጣታቸውን ጠቅሰው መንግስት በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ በሁሉም የቅድመ አንደኛ እና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ምገባና ዩኒፎርም ማቅረብን ጨምሮ የተለያዩ ድጋፎችን እያደረገ ወላጆችን ከከፍተኛ ወጪ አድኖ በማስተማር ላይ እንደሚገኝ በመግለጽ ወላጆችም በተለያዩ አካላት የሚፈጠሩ አሉባልታዎችን ወደ ጎን በማለት ከመንግስት የሚሰጡ መረጃዎችን መስማት እንደሚጠበቅባቸው አስረድተዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምገባ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አንቺነሽ ተስፋዬ በበኩላቸው በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ወደ 600,000 የሚሆኑ ተማሪዎች የምገባ አገልግሎት በማግኘት ላይ መሆናቸውን ገልጸው ይህንን አገልግሎት 10,000 የተማሪ ወላጅ እናቶች ተደራጅተው መርሀ ግብሩን በኃላፊነት በማከናወን ላይ መሆናቸውን አስገዝበዋል።

ዳይሬክተሯ አክለውም ሀና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተማሪ ወላጆች በ10 ማህበራት ተደራጅተው የምገባ አገልግሎቱን በመስጠት ላይ እንደሚገኙ ጠቅሰው አንዳንድ ሚዲያዎች ጉዳዩ ከሚመለከተው አካል መረጃ ሳይወስዱ ባሰራጩት የተዛባ መረጃ ህብረተሰቡን መረበሻቸውን አስታውቀዋል።

የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ ዳክተር ሙልጌታ እንዳለ 714 ተማሪዎች ወደ ህክምና ማዕከላት ሄደው በተደረገላቸው ምርመራ 7 ተማሪዎች ላይ ከታየ የማስመለስ ምልክት በስተቀር በሌሎቹ ላይ ምንም አይነት ከምግብ መመረዝ ጋር የተገናኘ ችግር እንዳላጋጠመ ጠቅሰው የሰባቱ ተማሪዎች የድምና ሰገራ ናሙና ተወስዶ ተጨማሪ ምርመራ እየተደረገ መሆኑንና ውጤቱም እንደታወቀ ለህብረተሰቡ እንደሚገለጽ አስረድተዋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

በመንግሰት የፋይናንስ አሰራር ስርዓት ዙሪያ ምክክር ተካሄደ

ቀን 21/06/2008 ዓ.ም
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የክፍያና ሂሳብ ደጋፊ የስራ ሂደት ከአዲስ አበባ ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ጋር በመተባበር መሰረታዊ በሆኑ የመንግሰት ፋይናንስ አሰራር ስርዓቶች ዙሪያ ከቢሮዉ መካከለኛ አመራሮችና ከየስራ ሂደቱ የተወሰኑ በተለይም ከዝክረ ሃሳብ (proposal) ዝግጅትና ፋይናንስ ስራ ጋር ተያያዥ የሆኑ ስራዎችን የሚሰሩ ባለሙያዎች በድምሩ 60 ከሚሆኑ ተሳታፊዎች ጋር ለሁለት ቀናት የቆየ የግንዛቤ መስጨበጫ ምክክር አካሄደ፡፡
የምክክር መድረኩ ዋነኛ አላማ በትምህርት ልማት ዘርፍ በተሰማሩ የትምህርት አመራሮችና ባለሙያዎች ዙሪያ ዘርፈ ብዙ የአቅም ግንባታ ስራዎች የሚሰሩና ከዚህ ጋር ተያይዞ በሚደረገዉ የፋይናንስ ክፍያ ስራና የዝክረ ሃሳብ አዘገጃጀት ላይ በተደረገ ዳሰሳዊ ጥናት ከፋይናንስ አሰራር ጋር የተለያዩ ጉዳዮች ብዥታ የፈጠሩበት ሁኔታ በስፋት የተስተዋለ መሆኑን በመገንዘብ የፋይናንስ አሰራሩን ወጥ ለማድረግና ግልጽነትን ለመፍጠር ታስቦ የተዘጋጀ መድረክ መሆኑን በትምህርት ቢሮ የክፍያና ሂሳብ ደጋፊ የሥራ ሂደት ባለሙያ አቶ መክብብ በለጠ ገልጸዋል ፡፡
በተካሄደዉ የምክክር መድረክ ላይ የመንግስት የገንዘብ ክፍያ መርሆች፣ የጥሬ ገንዘብ አስተዳደር ስርዓት አጠቃላይ ገጽታ፣ በፋይናንስ አሰራሮችና ሌሎች ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ከመድረክ አቅራቢዎች ሰፋ ያለ ገለጻ ተደርጓል፡፡ እንደ ተግዳሮት ከተነሱት ነጥቦች መካከል ለክፍያ የሚቀርቡ ዝክረ ሃሳቦች ተገቢዉን መስፈርት ያለሟሟላት፣ የስልጠና ተሳታፊዎች ሰዓት መቆጣጠሪያን በአግባቡ አለመከታተል፣ክፍያን በወቀቱ ቀርቦ ባለመቀበል ሂሳብ ለማወራረድ መቸገርና የመሳሰሉት አስተያየቶች በትምህርት ቢሮ የክፍያና ሂሳብ ደጋፊ ስራ ሂደት ክፍል ቀርበዉ በተሳታፊዎች ሰፋ ያለ ዉይይት ተካሄዶባቸዋል፡፡ የተነሱት ችገሮች በሁሉም ስራ ሂደቶች ላይ የሚስተዋሉ ባይሆንም በአብዛኛዎቹ የስራ ሂደቶች የሚታዩ ችግሮች እንደመሆናቸዉ ከላይ የተጠቀሱትንና ሌሎች ችገሮችን ቀጣይ በሚሰሩ ስራዎች ላይ ትኩረት በመስጠት መቅረፍ እንደሚገባ ተጠቅሷል፡፡
የትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ሃላፊ አቶ ሃይለስላሴ ፍሰሃ በማጠቃለያ መርሃ ግብር ላይ ተገኝተዉ እንደገለጹት ለተቋሙ የተመደበውን በጀት አጠቃቀም መመሪያን ጠንቅቆ ማወቅና በስራም ላይ ተግበራዊ ማድረግ የሁሉም የስራ ሂደቶች ሃላፊነት መሆኑን በማስገንዘብ የምክክር መድረኩ መዘጋጀቱ ተገቢ መሆኑን ጠቅሰዉ ፣ በቢሮዉ ያሉ ሰራ ሂደቶች ለሚያዘጋጁት ስልጠናም ሆነ ሌሎች መድረኮች የሚያስፈለጉ ወጪዎችን በተመለከተ የፋይናስ ስርዓትን መሰረት ያደረገ አሰራርን እንዲከተሉና ለሰራ የሚወጡ ወጪዎች ለሚመለከተዉ አካልና ለሚፈለገዉ ዓላማ ብቻ መዋሉን በጥብቅ መከታተል እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡
በማጠቃለያም ተሳታፊዎች ከምክክር መደረኩ ለቀጣይ ስራ መሻሻል ጠቃሚ መረጃዎችን ማግኘት መቻላቸዉንና በተገኘዉ ልምድ መሰረት እንደሚሰሩ ጠቅሰዉ ለሁለቱ ቀናት ሲደረግ ስለነበረዉ የምክክር መድረክ አጠቃላይ ሁኔታና ለወደፊት ሊስተካከሉ በሚገቡ የፋይናንስ አሰራሮች ዙሪያ ሀሳብ በመለዋወጥ፤እንዲሁም በክፍያና ሂሳብ ደጋፊ ሰራ ሂደት የቀረቡ መጠይቆች ላይ አሰተያየት በመሥጠት የመርሃ ግበር ፍጻሜ ሆኗል፡፡