ቀን 22/5/2015 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መምህራን  ማህበር ለማህበሩ አመራሮች የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና መስጠት ጀመረ::

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መምህራን ማህበር ከአደስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ጋር በጋራ በመሆን የአመራር ክህሎትና በራስ ስብዕና ግንባታ ላይ ያተኮረ ስልጠና መስጠት ጀምራል::

በስልጠናው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መምህራን ማህበሩ ፕሬዝዳንት አቶ ድንቃለም ቶሎሳ የክህሎት ማዳበሪያ ስልጠናው ለትምህርት ጥራትና ለተቋሙ ስኬት የሚያግዝ መሆኑን ተናግረዋል :: ስልጠናውም ተቋምን በመቀየር ሂደት የአመራሩ ሚና ምን መሆን እንዳለበት ግንዛቤ እንደሚሰጥ ገልፀዋል ::

ሰልጣኞች በስነባህሪ ግንባታ ራሳቸውን በመለወጥ ሌሎችን ማሰልጠን እንደሚጠበቅባቸው የገለፁት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመምህራን ማህበር ትምህርት ስልጠናና ምርምር ዘርፍ ኃላፊ አቶ ታረቀኝ ወ/ሃና የተለወጠ የሰው ኃይል በማፍራት የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መቅረፍ የስልጠናው ዋና አላማ መሆኑን አስረድተዋል ::

ለሶስት ቀናት በሚቆየው ስልጠና 440 የሚሆኑ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያሉ የመሰረታዊ መምህራን ማህበር ሰብሳቢዎች እንዲሁም የክፍለ ከተማና የቴክኒክና ሙያ መዋቅር ሥር ያሉ የክፍለ ከተማ መምህራን ማህበር አመራሮች እንደሚሳተፉ ከማህበሩ ያገኘነው መረጃ ያሳያል::

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ቀን 19/5/2015 ዓ.ም

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የተመዘገበው ውጤት የተሻለ መሆኑ ተመላከተ፡፡

በ2014 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከወሰዱ 896,520 ተማሪዎች መካከል፡-  

  1. 50 ከመቶ እና በላይ  ውጤት ያመጡ ተማሪዎች 3.3 በመቶ ሲሆኑ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፈተናውን ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 19.8 ፐርሰንት ተማሪዎች 50 እና በላይ ማለፊያ ውጤት ማስመዝገብ መቻላቸው፤
  • በሀገር አቀፍ ደረጃ 600 እና በላይ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች ቁጥር 273 ሲሆን ከእነዚህ ተማሪዎች መካከል 125 ተማሪዎች በከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ ውጤት ማምጣታቸው፤
  • እንደ ሀገር እጅግ ከፍተኛ ውጤት ካስመዘገቡ 20 ትምህርት ቤቶች መካከል ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር  10 ትምህርት ቤቶች እጅግ ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገባቸው፤

በአጠቃላይ የከተማ አስተዳደሩ ተፈታኝ ተማሪዎች በሀገር አቀፍ ደረጃ ከተመዘገበው ውጤት አንጻር በጣም አስደሳችና አበረታች ውጤት አስመዝግበዋል፡፡ ይሁን እንጂ ውጤቱ ገና የሚቀረው በመሆኑ በቀጣይ ከዚህ የላቀ ውጤት ማስመዝገብ እንዲቻል የትምህርት ባለድርሻ አካላት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳትሉ የሚናችሁን እንድትወጡ አደራ እያልን ለተመዘገበው ከፍተኛ ውጤት እንኳን ደስ አላችሁ! ለማለት እንወዳለን፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ቀን 19/5/2015 ዓ.ም

በ2014 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከወሰዱ 896 ሺህ 520 ተማሪዎች መካከል ከ50 በመቶ በላይ ያመጡ ተማሪዎች ቁጥር 29 ሺህ 909 ተማሪዎች መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።

የ2014 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ላይ ሪፖርትና ዋና ዋና ግኝቶች በትምህርት ሚኒስቴር መግለጫ ተሰጥቷል።

የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ የፈተና አሰጣጡ ከዚህ ቀደም ከነበሩት የተለየ እንደነበርና በሁሉም የሚመለከታቸው አካል ርብርብ በስኬት የተጠናቀቀ እንደነበር አንስተዋል።

በፈተና ወቅትም ምንም አይነት ስርቆት ሳይደረግ የተጠናቀቀ ሲሆን አሁን የተለቀቀው ውጤትም በፈተና ወቅት ሲኮርጁ የነበሩ ተማሪዎችን በማውጣት በስርዓቱ የተፈኑ ተማሪዎችን ብቻ ያካተተ መሆኑን አስታውቀዋል።

በአጠቃላይ ለፈተናው 985 ሺህ 384 ተማሪዎች የተመዘገቡ ሲሆን ከዚህ ውስጥ የተፈተኑና ውጤታቸው የተያዘላቸው ተማሪዎች ቁጥር 896 ሺህ 520 መሆኑን አስረድተዋል።

ከዚህ ውስጥ በፈተናው ተመዝግበው ያልተገኙ 77 ሺህ 98 ተማሪዎች ሲሆኑ 20 ሺህ 170ዎቹ ደግሞ በፈተናው ተገኝተው በተለያዩ የደንብ ጥሰቶች እንዳይፈተኑ የተደረጉና ፈተናውን ትተው የሄዱ ተማሪዎች ናቸው ብለዋል።

በአጠቃላይ በወጣው የፈተና ውጤትም በሀገር አቀፍ ደረጃ የተገኘው አማካይ ውጤት 29 ነጥብ 5 በመቶ ነው።

በመግለጫውም፥ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተመዘገበው ከፍተኛ ውጤት ከሰባት መቶ 666 በተፈጥሮ ሳይንስ ሲሆን፤ ከማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ ከስድስት መቶ 524 መመዝገቡ ተጠቅሷል።

በተፈጥሮ ሳይንስ 600 እና ከዛ በላይ ያስመዘገቡ 263 ተማሪዎች መኖራቸውም በመግለጫው ላይ ተመልክቷል።

በማህበራዊ ሳይንስ በአጠቃላይ 500 እና ከዛ በላይ ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ 10 ተማሪዎች መሆናቸውም ተጠቅሷል።

ፈተናውን ከወሰዱ ተማሪዎች ውስጥ ከ50 በመቶ በላይ ያመጡ ተማሪዎች ብዛት 29 ሺህ 909 ሲሆን ይህም ከአጠቃላይ ተፈታኞች 3 ነጥብ 3 በመቶ ነው ተብሏል።

ሚኒስትሩ ይህ የፈተና ውጤት ለዓመታት ሲንከባለል የቆየ የበርካታ ችግሮች መገለጫ እና ተሸፍኖ የቆየውን እውነተኛ የትምህርት ስርዓተ ያለበትን ደረጃ ያመላከተ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

ለዚህም ተጠያቂው ከመንግስት ጀምሮ ሁሉም የትምህርት ማህበረሰቡ መሆኑንም ነው የገለጹት።

ይህን ውጤት ለመቀየር አጠቃላይ ሀገር አቀፍ የትምህር ስርዓቱን ለመቀየር አዲስ ስትራቴጂን ለማዘጋጀት መታቀዱን አስታውቀዋል።

ከ50 በመቶ በታች ያመጡ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ እንደማይቀላቀሉ የተገለጸ ሲሆን ነገር ግን የዩኒቨርሲቲዎችን የመቀበል አቅም ከግምት ውስጥ በማስገባት በውጤታቸው መሰረት ተጨማሪ ተማሪዎችን በመቀበል ለቀጣይ ዓመት ዩኒቨርሲቲ መግባት የሚያስችላቸውን ውጤት እንዲያገኙ ይሰራል መባሉን ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ዘግባል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ቀን 19/5/2015 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የስርዓተ ጾታ ማስረጽና ማካተት ዳይሬክቶሬት ማህበራዊ ሚዲያዎችን በመጠቀም የሚከሰቱ ጾታዊ ጥቃቶችን ለመከላል የሚያስችል ስልጠና ሰጠ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የስርአተ ጾታ ማስረጽና ማካተት ዳይሬክቶሬት ከUnicef ጋር በመተባበር ማህበራዊ ሚዲያዎችን በመጠቀም የሚከሰቱ ጾታዊ ጥቃቶችን ለመከላል የሚያስችል ስልጠና ሰጥቷል፡፡

በስልጠናው የመድኃኒዓለም አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የአይሲቲና እንግሊዘኛ ቋንቋ መምህራን የተሳተፉ ሲሆን ስልጠናውን መውሰዳቸው መምህራኑ በማህበራዊ ሚዲያዎች የሚደርሱ ጾታዊ ጥቃቶችን ለመከላከል የተማሪዎች የራሳቸውን በጎ ተፅእኖ ማሳደር እንዲችሉ ያስችላል ተብሏል ።

በስልጠናው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የስርዓተ ጾታ ማስረጽና ማካተት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ አበባ ዘውዴ እንዳሉት ስልጠናው ተማሪዎች በተለይም ሴቶች በማህበራዊ ሚዲያዎች በመጠቀም የሚደርሱ ፆታዊ ጥቃቶችን ለመከላከል መምህራን እገዛ እንዲያደርጉ ያስችላል ብለዋል::

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ቀን 18/5/2015 ዓ.ም

ለ2014 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና  ውጤት ከሌሊቱ 5 ሰዓት ከ30 ጀምሮ ይፋ ይሆናል።

ለ2014 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና  ውጤት ሌሊቱ 5 ሰዓት ከ30 ጀምሮ ይፋ እንደሚሆን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታወቀ።

በዚህም ተፈታኞች ከዛሬ ሌሊቱ 5 ሰዓት ከ30 ጀምሮ በዌብ ሳይት https://eaes.edu.et/ ፣ በ6284 አጭር የጽሑፍ መልዕክት መላኪያ ላይ የምዝግባ ቁጥራቸውን (Registration Number) ብቻ በመላክ ወይም  በቴሌግራም  https://t.me/eaesbot ማየት የሚችሉ መሆኑን ተገልጿል።

 ማሳሰቢያ፡-

• ማንኛውም ቅሬታ ያላቸው ተፈታኞች በአካል መምጣት ሳያስፈልግ እስከ ጥር 26/2015 ዓ.ም ድረስ በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዌብ ሳይት https://eaes.edu.et/ ላይ Compliant የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ማቅረብ ይችላሉ፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ቀን 17/5/2015 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የስድስት ወራት እቅድ አፈፃፀም ተመዘነ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፕላን ኮሚሽን በ2015 ዓ.ም በከተማ አስተዳደሩ የሚገኙ ተቋማትን የስድስት ወራት እቅድ አፈፃፀም በመመዘን ላይ የሚገኝ ሲሆን በዛሬው እለት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በመገኘት የቢሮውን የ2015 የትምህርት ዘመን የስድስት ወራት እቅድ አፈጻጸምን መዝኗል።

በምዘናው በ2015 የትምህርት ዘመን በመጀመሪያው ስድስት ወራት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሊከናወኑ በእቅድ የተነደፉ ተግባራትን አፈጻጸም ሰነዶችን በመፈተሸ እና በአካል ወርዶ በማየት ምዘናው ተከናውናል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የእቅድ ዝግጅትና ክትትል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ጌታሁን ለማ  ምዘናው ማስረጃ ሰነዶችን መሠረት ያደረገና በተጨባጭ ማስረጃ ላይ ተመሰርቶ መከናወኑን ገልጸዋል፡፡ አቶ ጌታሁን አክለውም  የምዘና ሂደቱ ጥሩ እንደነበር ገልፀው መዛኝ ቡድኑም መረጃዎችን በተለያዩ አማራጮች ለማረጋገጥ የሄዱበትን ርቀት አድንቀዋል።

የመዛኝ ቡድን አባላቱ በበኩላቸው በተቋሙ ያሉ የስራ መሪዎች ለምዘናው የሰጡት ግምት እና መረጃዎችን በተጠየቀው ልክ ለማቅረብ ላሳዩት ተነሳሽነት ምስጋና አቅርበዋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ቀን 15/5/2015 ዓ.ም

አዲሱ የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ በትምህርቱ ዘርፍ ላይ መሠረታዊ ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉ ጉዳዮችን ያካተተ እንደሆነ ተገለፀ፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር በአዲሱ የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ ረቂቅ ላይ  ከምሁራን ጋር ምክክር እያካሄደ ነው ።

የምክክር መድረኩን በንግግር የከፈቱት የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ(ፕ/ር)  ረቂቅ ፖሊሲው በተለያዩ ጊዜያት ምክክር ሲደረግበት የቆየ መሆኑን እና በትምህርቱ ዘርፍ መሠረታዊ ለውጥ ያመጣሉ ተብለው የታሰቡ ጉዳዮችን ያካተተ መሆኑን ገልፀዋል።

በትምህርት ሥርዓቱ የደረሰውን ስብራት ለማከም ፖሊሲ መቅረፅ ብቻውን ለውጥ አያመጣም ያሉት ሚኒስትሩ ያሉ ስብራቶችን በሙሉ ለመቅረፍ በጋራ መሥራት እንደሚጠበቅም ገልፀዋል።

ፓሊሲው በትምህርትና ስልጠና ፍኖተ ካርታው  የቀረቡ ምክረ ሀሳቦችን በመመልከት በትምህርቱ ዘርፍ ያሉ ተግዳሮቶችን  ሊፈታ በሚችልና አለም አቀፍ ስታንዳርዱን በጠበቀ መልኩ መዘጋጀቱም ተገልጿል። በቀጣይም የፖሊሲ ማስፈፀሚያ ስትራቴጂዎች፣ የህግ ማዕቀፎች እና ፕሮግራሞች እንደሚዘጋጁም ነው የተነገረው።

ፓሊሲውን ለመተግበርም የመንግስት ብቻ ሳይሆን የሁሉንም ተሳትፎ እንደሚጠይቅም በመድረኩ ተነስቷል። የረቂቅ ፖሊሲው ዋና ዋና ሀሳቦች የትምህርት  ሚኒስትር የስርዓተ ትምህርት ማበልፀጊያ መሪ ስራ አስፈፃሚ በሆኑት ቴዎድሮስ ሸዋርገጥ (ዶ/ር)  ቀርቦ ውይይትም ተደርጎበታል።

በምክክር መድረኩ ላይ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፣ ከስራና ክህሎትና ሌሎች ሚኒስቴር መ/ቤቶች፣ ከክልል ትምህርት ቢሮዎች፣ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ከመምህራን ማህበር፣ ከትምህርት አማካሪ ምክር ቤት፣ የተለያዩ የሞያ ማህበራትና ሌሎች አጋር ተቋማት የተውጣጡ አካላት በመሳተፍ ላይ መሆናቸውን የትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ቀን 12/5/2015 ዓ.ም

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ!

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በ13/02/2015 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ባወጣው የቅድመ አንደኛ ደረጃ መምህርነት ቅጥር ማስታወቂያ መሰረት የተመዘገባችሁና ፋይላችሁ በቀን 04/05/2015 ዓ.ም የተጣራ ስማችሁ ከዚህ በታች በቢሮው የ (Telegram and Facebook) አድራሻ ላይ የተገለጻችሁ መምህራን ብቻ ማንነታችሁን የሚገልፅ መታወቂያ በመያዝ ሰኞ በ15/05/2015 ዓ.ም 3፡30 ሰዓት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አዳራሽ ፈተና የሚሰጥ ስለሆነ በሰዓቱ እንድትገኙ እናሳውቃለን፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ቀን 10/5/2015 ዓ.ም

ለክርስትና ዕምነት ተከታዩች በሙሉ እንኳን ለጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ! 

የጥምቀት በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ ሀይማኖታዊ ትውፊቱን ጠብቆ በየዓመቱ በደማቅ ስነ-ስርዓት የሚከበር ክብረ በዓል ከመሆኑም ባሻገር ማህበራዊ ትስስርን የሚያጠናክር ማህበራዊ እሴት ነው፡፡ይህ ደግሞ ፍቅርን በማብዛት፣ ወንድማማችነትን በማሳደግ እና እርስ በእርስ መተዛዘንን በማጠናከር ለሀገር ግንባታ ትልቅ መሳሪያ ሆኖ ያገለግላል።

የጥምቀት በዓል በዩኔስኮ በማይዳሰሱ ቅርሶች በአለም ቅርስነት የተመዘገበ በአለም አደባባይ የምንታወቅበት ድንቅ ባህላችን ነው። በዓሉ የሀገራችን ብቻ ሳይሆን አለም በድምቀት የሚያከብረው የጋራ ኩራታችን የሆነ ታላቅ በዓላችን በመሆኑ ክብረ በዓሉ ሀይማኖታዊ ስርዓቱን ጠብቆ በሠላም እንዲጠናቀቅ ሁላችንም ኃላፊነታችንን መወጣት አለብን።

በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ ጥር 10 እና 11 ቀን የሚከበሩት የከተራ እና የጥምቀት በዓላት ከሃይማኖታዊ በዓልነት ባሻገር የሀገርን መልካም ገጽታን ከመገንባት እና የቱሪስት ፍሰትን ከማጎልበት አንጻር ጉልህ ሚና የሚጫወቱ በመሆኑ እንግዶችን በፍቅር ተቀብሎ በማስተናገድ በዓሉ በሰላም ተጀምሮ በሰላም እንዲጠናቀቅ ህብረተሰቡ በተለይም ደግሞ የትምህርት ባለድርሻ አካላት ከፀጥታ አካላት ጋር እጅና ጋንት በመሆኑ መስራት ይኖርባችዋል።

በመጨረሻም ለክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለአየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት በሰላም አደረሳችሁ!

በዓሉ የመተሳሰብ ፣ የመረዳዳት፣ የሰላም ፣ የፍቅር እና የጤና እንዲሆን እመኛለሁ፡፡

አመሰግናለሁ!

ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ ደሙ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/