ቀን 19/ 4 / 2013 ዓ.ም

እንኳን ደስ አላችሁ! የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጤት ይፋ ሆናል፡፡

በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ዘግይቶ በ2013 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር  ትምህርት ቢሮ  በ156 የመፈተኛ ጣቢያዎች  ለ71,476 ተማሪዎች የተሰጠዉ  የ2012 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና  ውጤት ይፋ ሆናል፡፡

ለክልላዊ ፈተና ከተቀመጡ ተማሪዎች መካከልም 80 % ተማሪዎች ወደ ቀጣይ ክፍል የተዛወሩ ሲሆን የተሻለ ውጤትም  የተመዘገበ በመሆኑ ተማሪዎች ፣ ወላጆች በአጠቃላይ የትምህርት ባለድርሻ አካላት እንኳን ደስ አላችሁ ፡፡

የፈተናዉ ውጤትም ለ10ሩም ክፍለ ከተማዎች በዛሬዉ እለት የተሰራጨ ሲሆን ተማሪዎች ከነገ ጀምሮ  ውጤታችሁን በየትምህርት ቤቶቻችሁ መመልከት እንደምትችሉ ይጠበቃል፡፡

መረጃዎችን  በፍጥነት  ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

ባልታጠበ  እጅ  አይንዎን  አፍዎን  እና  አፍንጫዎን  ባለመንካት  በዙሪያዎ  ላሉ  ሰዎች  አርአያ  ይሁኑ!

ቀን 8 / 4 / 2013 ዓ.ም

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ4ኛ ዙር ከፊታችን ሰኞ ከታህሳስ 12/4/2013 ዓ/ም ጀምሮ ወደ ገጽ ለገጽ የመማር ማስተማር ስራ የሚገቡ የክፍል ደረጃዎችን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ይፋ አደረገ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ አቶ ዘላለም ሙላቱ ደሙ በዛሬዉ እለት በሰጡት መግለጫ እንዳሳወቁት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን እየተከላከሉ የገጽ ለገጽ የመማር ማስተማር ስራዉን በከተማዉ ለማስጀመር በተቀመጠዉ ውሳኔ መሰረት ቀደም ሲል ህዳር 16 የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል ተማሪዎቸ በክለሳ ትምህርት ውስጥ እንዳልፉ ፣  ህዳር 28 በግል ትምህርት ቤቶች ከ1 ክፍል ጀምሮ እና በመንግሰት ትምህርት ቤቶች ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ በሶስት ዙሮች መጀመሩን ገልጸዉ ከፊታችን ሰኞ ከታህሳስ 12/4/2013 ዓ/ም ጀምሮ በ4ኛ ዙር ወደ ገጽ ለገጽ የመማር ማስተማር ስራ የሚገቡ የክፍል ደረጃዎች በግል ትምህርት ቤቶች የቅድመ መጀመሪያ ደረጃ ተማሪዎች እና በመንግስት ትምህርት ቤቶች ከ1ኛ – 4ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች መሆናቸዉን ሀላፊዉ አሳውቀዋል፡፡

ሀላፊዉ በመግለጫቸዉ አክለዉም ህጻናት ተማሪዎችን ወደ ገጽ ለገጽ የመማር ማስተማሩ ስራ እያመጣን በመሆኑ የተዘጋጀዉን የኮቪድ ፕሮቶኮልን በአግባቡ መተግበር እንዲቻል የትምህርት ባለድርሻ አካላት የበኩላቸዉን ሚና እንዲወጡ ጥራቸዉን አቅርበዋል፡፡  

መረጃዎችን  በፍጥነት  ለማግኘት የዩቲዩብ ፣ የቴሌግራም ፣ የፊስቡክ እና  የትዊተር  ገፃችንን  ሰብስክራይብ  ያድርጉ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

ባልታጠበ  እጅ  አይንዎን  አፍዎን  እና  አፍንጫዎን  ባለመንካት  በዙሪያዎ  ላሉ  ሰዎች  አርአያ  ይሁኑ!

ቀን 1 / 4 / 2013 ዓ.ም

የጃፓን መንግስት በአዲስ አበባ ከተማ በቂርቆስ ክፈለ ከተማ በሚገኘዉ ጠመንጃ ያዥ እንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አምስት የመምህራን ክፍሎችና አንድ ቤተመጻሕፍት ለማስገንባት የ3 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር በዛሬዉ እለት ስምምነት አደረገ።

ስምምነቱን በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ሚስ ኢቶ ታካካና የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር አባተ ከልቤ ተፈራርመዋል።

የጃፓን መንግስት ከ1989 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ እያካሄደ ያለው የሰው ልጆች ማህበራዊ ዋስትና ፕሮጀክት አካል የሆነው ይህ ግንባታ በአንድ አመት ጊዜ የሚጠናቀቅ መሆኑም ተጠቁሟል።

በዚህ የሰው ልጆች ማህበራዊ ዋስትና ፕሮጀክት አማካኝነት የጃፓን መንግስት በትምህርት፣ በጤና፣ በንጹህ መጠጥ ውሃ፣ በንጽህና አጠባበቅ፣ በምግብ ዋስትናና በሌሎች የማህበራዊ ዋስትና መስኮች ከ1989 ጀምሮ ከ400 በላይ የሚሆኑ ፕሮጀክቶችን አጠናቆ አስረክቧል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የዩቲዩብ ፣ የቴሌግራም ፣ የፊስቡክ እና የትዊተር ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!
You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 28 / 3 / 2013 ዓ.ም

መረጃዎችን  በፍጥነት  ለማግኘት የዩቲዩብ ፣ የቴሌግራም ፣ የፊስቡክ እና  የትዊተር  ገፃችንን  ሰብስክራይብ  ያድርጉ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

ባልታጠበ  እጅ  አይንዎን  አፍዎን  እና  አፍንጫዎን  ባለመንካት  በዙሪያዎ  ላሉ  ሰዎች  አርአያ  ይሁኑ!

ቀን 25 / 3 / 2013 ዓ.ም

በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት የዘገየው እና በትላንትናው ዕለት የተጀመረው የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና  በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሚገኙ 156 የፈተና ጣቢያዎች ዛሬም በዚህ  መልኩ ቀጥሎ እየተሰጠ ይገኛል፡፡

መረጃዎችን  በፍጥነት  ለማግኘት የዩቲዩብ ፣ የቴሌግራም ፣ የፊስቡክ እና  የትዊተር  ገፃችንን  ሰብስክራይብ  ያድርጉ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

ባልታጠበ  እጅ  አይንዎን  አፍዎን  እና  አፍንጫዎን  ባለመንካት  በዙሪያዎ  ላሉ  ሰዎች  አርአያ  ይሁኑ!