ቀን 19/2/2015 ዓ.ም

የቀዳማይ ልጅነት እድገትና እንክብካቤ ፕሮጀክት የቦርድ አባላት በቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የመስክ ምልከታ አካሄዱ።

የመስክ ምልከታው አራዳ ክፍለ ከተማ በሚገኙት ዳግማዊ ሚኒሊክ እና ገነት ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተካሄደ ሲሆን በጉብኝቱ የቀዳማይ ልጅነት እድገትና እንክብካቤ ፕሮጀክት የቦርድ ሰብሳቢ ጄሚ ኩፐር፣የፕሮጀክቱ አባልና የቀድሞው ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ዶክተር ከሰተብርሀን አድማሱ፣የከንቲባ ጽህፈት ቤት ኃላፊው አቶ ጥላሁን ወርቁን ጨምሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ፣የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዮሀንስ ጫላ እንዲሁም የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ዶክተር ታቦር ገብረመድህን እና ሌሎች ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ተሳታፊ ሆነዋል።

የጉብኝቱ ተሳታፊዎች በዋናነት በትምህርት ቤቶቹ ያለውን  የትምህርት አሰጣጥ እንዲሁም የተማሪዎችን የማሸለቢያና የመመገቢያ ክፍሎች ከማየታቸው ባሻገር ለቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራን የሚሰጠውን የአቅም ግንባታ ስልጠና ተመልክተዋል።

በተያያዘ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ከቀዳማይ ልጅነት እድገትና እንክብካቤ ፕሮጀክት ጋር በመተባበር በ9 የስልጠና ጣቢያዎች ለሁለተኛ ዙር የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰቷል።

ስልጠናው ለቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራን የተዘጋጀ የማሰልጠኛ ማኑዋልን መሰረት አድርጎ ለ1,500 የአማርኛና አፋን ኦሮሞ መምህራን መሰጠቱን በትምህርት ቢሮ የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ወይዘሪት ትግስት ድንቁ ገልጸው ቀደም ሲል ለ1,102 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራን ተመሳሳይ ስልጠና መውሰዳቸውን አስታውቀዋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ቀን 18/2/2015 ዓ.ም

ኤች አይ ቪ ኤድስን መከላከል በሚያስችሉ ተግባራት ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ፡፡

ስልጠናው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ክትትልና ትግበራ ዳይሬክቶሬት አማከይነት ለሁሉም የቢሮው ሰራተኞች በሁለት ዙር በመሰጠት ላይ የሚገኝ ሲሆን በዛሬው እለት የመጀመሪያው ዙር ሰልጣኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናውን ወስደዋል፡፡ 

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ክትትልና ትግበራ ቡድን የኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ባለሙያ ወይዘሪት ገንዘብ ደሳለኝ በስልጠናው ባስተላለፉት መልዕክት የኤች አይ ቪ ኤድስ ስርጭትን ለመቆጣጠርም ሆነ ለመከላከል በየደረጃው ከሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር በጉዳዩ ዙሪያ ውይይት በማስፈለጉ ለቢሮው ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው መዘጋጀቱን ገልጸው በቫይረሱ የሚያዙ የህብረተሰብ ክፍሎች ቁጥር አሁንም ቢሆን እየጨመረ ስለሆነ ለቫይረሱ ተጋላጭ የሆኑ አካላትን ተጋላጭነት ለመቀነስ የአመለካከት ለውጥ ማምጣት እንደሚገባ አስረድተዋል።

ባለሙያዋ አክለውም የትምህርት ሴክተሩ የኤች አይ ቪ ኤድስ ስርጭትን ከመከላከልና ከመቆጣጠር አንጻር ከፍተኛ ስራ መስራት ከሚጠበቅባቸው ተቃማት መካከል አንዱ መሆኑን ጠቁመው በትምህርት ቤቶች የሚገኙ  ተማሪዎች ለችግሩ ተጋላጭ እንዳይሆኑ የትምህርት ባለድርሻ አካላት በጋራ መስራት እንደሚጠበቅባቸው አስታውቀዋል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ቀን 18/2/2015 ዓ.ም

የተማሪዎች ፣ የመምህራን እና የርዕሳነ መምህራን የሳይንስ ሙዚየም ትምህርታዊ ጉብኝት

በልደታ ክፍለ ከተማ በወረዳ 11 ስር የሚገኘው የልማት ምንጭ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት የ2015 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች፣ መምህራን እና ርዕሳነ መምህራን በቅርቡ የተመረቀውን የሳይንስ ሙዚየም ትምህርታዊ ጉብኝት ማካሄዳቸውን ከትምህርት ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያሳያል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ቀን 17/2/2015 ዓ.ም

ማስታወቂያ!

የአዲሰ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት በ12/02/2015 ዓ.ም የምግብ ጥራት አቅርቦት ቁጥጥር ባለሙያ ፈተና ተፈትናችሁ ያለፋችሁ ስማችሁን ሊንኩን          በመጫን መመልከት የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ከሚቀዕለው ሳምንት ጀምሮ በተመደባችሁበት ክፍለ ከተማ ሪፖርት እንድታደርጉ አናሳስባለን፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ቀን 15/2/2015 ዓ.ም

የሠራዊት ቀን በትምህርት ቤቶች “የጥንካሬያችን ምንጭ ሕዝባችን ነው!” በሚል መሪ ቃል ተከበረ፡፡

በየዓመቱ ጥቅምት 15 ቀን የሚከበረው የሠራዊት ቀን “የጥንካሬያችን ምንጭ ሕዝባችን ነው!” በሚል መሪ ቃል በግልና በመንግስት ትምህርት ቤቶች በተለያዩ መርሀ-ግብሮች ተከበረ፡፡

የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት የተቋቋመበት ጥቅምት 15 ቀን 1900 ዓ.ም መነሻ በማድረግ የሠራዊት ቀን በየዓመቱ የሚከበር ሲሆን ዘንድሮ በትምህርት ቤቶች በተለያዩ መርሃ ግብሮች ተማሪዎች ፣ መምህራን ፣ የትምህርት ባለሙያዎች እና የሰራዊት አባላት በተገኙበት በድምቀት ተከብራል፡፡  

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ቀን 13/2/2015 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አዲሱን የቅድመ አንደኛ ደረጃ ስርዓተ ትምህርት ለመምህራን አስተዋወቀ።

በማስተዋወቂያ መርሀ ግብሩ ዘንድሮ ስርዓተ ትምህርቱ በሙከራ ደረጃ ተግባራዊ ከሚደረግባቸው በአማርኛ ከ22 እና በአፋን ኦሮሞ ከ22 በጥቅሉ ከ44 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመጡ መምህራን እና የዘርፉ ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ስርዓተ ትምህርት ዝግጅትና ትግበራ ባለሙያ አቶ ነጋ ገረመው አዲሱ ስርአተ ትምህርት የሙከራ ትግበራ በሚደረግባቸው የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሚያስተምሩ 500 የሚሆኑ የደረጃ 1፣2እና 3 መምህራን እንዲተዋወቁ መደረጉን ገልጸው መምህራኑም በስርአተ ትምህርቱ የተቀመጡ መርሀ ትምህርቶችንም ሆነ ይዘቶቹን በአግባቡ ተረድተው ለህጻናቱ ተገቢውን ዕውቀት ማስጨበጥ እንደሚጠበቅባቸው አስታውቀዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአፋን ኦሮሞ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት አስተባባሪ አቶ አለማየሁ ጣሰው በበኩላቸው በስርዓተ ትምህርት የማስተዋወቂያ መርሀ ግብሩ 309 የሚሆኑ የአፋን ኦሮሞ ቅድመ አንደኛ ደረጃ መምህራን ተሳታፊ መሆናቸውን ጠቁመው መምህራኑ የሙከራ ትግበራ ከሚደረግባቸው ትምህርት ቤቶች የመጡ እንደመሆናቸው የመለማመጃ ደብተሩን ይዘትም ሆነ የመምህር መምሪያውን ተገንዝበው ተማሪዎቻቸው በአግባቡ ማስተማር እንዲችሉ በማሰብ የማስተዋወቂያ መርሀ ግብሩ መዘጋጀቱን አስረድተዋል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ቀን 12/2/2015 ዓ.ም

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ለመፈተን ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የመጡ የፈተና አስፈጻሚዎችን በከተማው የሚገኙ ታላላቅ ፕሮጀክቶችን አስጎበኘ።

ጉብኝቱ በዋናነት በእንጦጦና አንድነት ፓርክን ጨምሮ በወዳጅነት አደባባይና በቅርቡ ለዕይታ በበቃው የሳይንስ ሙዚየም የተካሄደ ሲሆን በጉብኝቱ 1200 የሚሆኑ የፈተና ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳኘው ገብሩ በጉብኝት መርሀ ግብሩ ባስተላለፉት መልዕክት በከተማ አስተዳደሩ ፈተናው በተሰጠባቸው 9 የፈተና ጣቢያዎች ፈተናው ያለምንም እንከን እንዲጠናቀቅ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ለተወጡ ፈታኞች ምስጋና አቅርበው ከተማ አስተዳደሩ በትምህርት ቢሮ አማካይነት የሸገር ማስዋብ አካል የሆኑ ትላልቅ ፕሮጀክቶችን የፈተና አስፈጻሚዎች እንዲጎበኙ በማድረጉ ከፍተኛ ደስታ እንደሚሰማው አስታውቀዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሩ አቶ ዲናኦል ጫላ በበኩላቸው ቢሮው የፈተና አስፈጻሚዎቹን በከተማው የሚገኙና የቱሪስት መዳረሻ የሆኑ ፕሮጀክቶችን ከማስጎብኘቱ ባሻገር ፈተና አስፈጻሚዎቹ በአዲስ አበባ ቆይታቸው ፈተናውን ያለምንም ችግር እንዲያስፈጽሙ የመኝታና የምግብ አገልግሎት ሲሰጥ መቆየቱን ጠቅሰው ፈተና አስፈጻሚዎቹም ከአቀባበል ጀምሮ በተደረገላቸው መስተንግዶ ለከተማ አስተዳደሩ እና ለትምህርት ቢሮ ምስጋና ማቅረባቸውን አስረድተዋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ቀን 11/2/2015 ዓ.ም

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከጥቅምት 8/2015 ዓ.ም ጀምሮ ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ሲሰጥ የቆየው የ12ኛ ክፍል መልቂያ ፈተና በሰላም ተጠናቀቀ፡፡

ፈተናው በአዲስ አበባ በ9 የፈተና ጣቢያዎች ሲሰጥ መቆየቱን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዲናኦል ጫላ ገልጸው ፈተናውን 24,987 ተማሪዎች መውሰዳችን አስታውቀዋል፡፡

አቶ ዲናኦል አክለውም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 47,520 የማህበራዊና የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የዘንድሮውን ፈተና መውሰዳቸውን ጠቁመው ፈተናውን ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ያልወሰዱና ተገቢ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ ተማሪዎች በቀጣይ እንደሚፈተኑ በትምህርት ሚኒስቴር በኩል አቅጣጫ መቀመጡን አስረድተዋል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር  በተዘጋጁ 9 የፈተና ጣቢያዎች 1600 የፈተና አስፈጻሚዎች ተሳታፊ መሆናቸውን አቶ ዲናኦል ገልጸው ፈታኞቹ ከተለያዩ የሀገሪቱ አከባቢዎች እንደመምጣታቸው ከተማ አስተዳደሩ የምግብና የመኝታ አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረጉን አስታውቀዋል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ቀን 10/2/2015 ዓ.ም

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የተሰጥኦ ማበልጸጊያ ትምህርት ቤትን መርቀው ከፈቱ፡፡

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቡራዩ ከተማ የተገነባውን የተሰጥኦ ማበልጸጊያ ትምህርት ቤት መርቀው ከፍተዋል።

የተሰጥኦ ማበልጸጊያ ትምህርት ቤቱ ልዩ ችሎታ ያላቸው ኢትዮጵያውያን ተሰጥኦዋቸውን የሚያወጡበት መሆኑ ተገልጿል፡፡

አሁን ላይ በኢትዮጵያ በተለያየ ደረጃ ትምህርት ቤቶች  እና  ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በርካታ ባለተሰጥኦዎች መኖራቸው ተመላክቷል፡፡

እነዚህ ባለተሰጥኦዎች  ያላቸውን ተሰጥኦ አበልጽገው ወደ ምርትና አገልግሎት ለመቀየር ሲያስቡ የትምህርት ቆይታቸውን ማጠናቀቅ ግድ ይላቸዋል፣ አሊያም ምቹ ሁኔታ ሳይፈጠርላቸው ባክነው ይቀራሉ።

ዛሬ የተመረቀው የተሰጥኦ ማበልጸጊያ ትምህርት ቤትም ይህንን ችግር የሚቀርፍ መሆኑ ነው የተገለጸው፡፡

ትምህርት ቤቱ  ባለተሰጥኦዎችን በመለየት ከመደበኛ መማር ማስተማር ሳይለዩ ልዩ ተሰጥኦዋቸውን የሚያበለጽጉበት  ነው ተብሏል፡፡

ህንጻው ማደሪያ፣ የመመገቢያ አዳራሽ፣ የአስተዳደር ህንጻ ፣ የህክምና ማዕከል፣ መማሪያ ክፍሎች፣ ቤተ ሙከራ ፣ ቤተ መጽሐፍ እና ወርክ ሾፖች ያሉት መሆኑም ተጠቁሟል፡፡

በተጨማሪም ሁሉንም አገልግሎቶች የሚሰጡ ግብዓቶች የተሟሉለት መሆኑ በምረቃ መርሐ ግብሩ ላይ መገለጹን ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያሳያል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ቀን 10/2/2015 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የስራተ ጾታ ማስረጽ እና ማካተት ዳይሬክቶሬት በትምህርት ቤትና አካባቢ የሚፈጸም ጾታዊ ጥቃትን ለመከላከል እና ምላሽ ለመስጠት በሚያስችል መመሪያ አዘጋጀ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የስራተ ጾታ ማስረጽ እና ማካተት ዳይሬክቶሬት ከኢንጀንደር ሄልዝ ግብረ ሰናይ ድረጅት ጋር በጋራ በመሆን በትምህርት ቤትና አካባቢ የሚፈጸም ጾታዊ ጥቃትን ለመከላከል እና ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል መመሪያ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር አዘጋጀ፡፡

የመድረኩን አስፈላጊነት የገለጹት የቢሮ የስራተ ጾታ መስረጽና ማካተት ዳይሬክተር ወ/ሮ አበባ ዘውድ  በትምህርት ቤትና አካባቢ የሚፈጸም ጾታዊ ጥቃትን ለመከላከል እና ምላሽ ለመስጠት በሚያስችል መመሪያ በኢፊዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር መዘጋጀቱን ገልጸው መመሪያውን ወደ አዲስ አበባ ነባራዊ ሁኔታ ለመቀየር እንዲቻል ያለመ ነው ብለዋል፡፡

በዝግጅቱ ላይ ጉዳዩ የሚመለከታቸው የትምህርት ቢሮ ባለሙያዎች ፣ ከተለያዩ ተቋማት የመጡ ባለድርሻ አካላት ፣ የተመረጡ ተማሪዎች  እና የትምህርት ቤት ርዕሳነ መምህራን  እንዲሁም የኢንጀንደር ሄልዝ ግብረሰናይ ድርጅት ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/