ቀን 22/10/2014 ዓ.ም

አራብሳ አጸደ ህጻናትና የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ አገልግሎት ተግባራዊ በማድረግ ላይ መሆኑ ተገለጸ፡፡

ትምህርት ቤቱ ተግባራዊ ካደረጋቸው አገልግሎቶች መካከል አንዱና ዋነኛው ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር 9715 አጭር የጽሁፍ መልዕክት ማስተላለፊያ መስመርን በመጠቀም ከተማሪ ወላጆች፤መምህራንና ከትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ ጋር በቀላሉ ግንኙነት መፍጠር የተቻለበት አሰራር መሆኑን የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር አቶ ጌትነት ገብረሚካኤል ገልጸው አገልግሎቱም በትምህርት ቤት ደረጃ ተግባራዊ ሲደረግ በአዲስ አበባም ሆነ በሀገር በአቀፍ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑን አስታውቀዋል ፡፡ 

ርዕሰ መምህሩ አክለውም ትምህርት ቤቱ 8,500 ተማሪዎችን ተቀብሎ በማስተማር ላይ የሚገኝ እንደመሆኑ ቀደም ሲል ከተማሪ ወላጆች ጋር የነበረው ግንኙነት በደብዳቤ ስለነበር ለወረቀትና ቀለም ሲወጣ የነበረውን ከፍተኛ ወጪ ማስቀርት  ከማስቻሉ ባሻገር የሰው ጉልበትና የማባዣ ማሽን አቅምን በአግባቡ ለመጠቀም መቻሉን ገልጸው ለአገልግሎቱም በወር 2,800 ብር ለኢትዮ ቴሌኮም እንደሚከፈል አስረድተዋል፡፡

ትምህርት ቤቱ ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢንተርኔት አገልግሎት በመጀመሩ መምህራን በአይ ሲቲ ላብራቶሪ የሚፈልጉትን መረጃ ማግኘት ከመቻላቸው ባሻገር ትምህርት ቤቱ በውጭ ሀገር ከሚገኙ መሰል ትምህርት ቤቶች ጋር የስራ ግንኙነት ፈጥሮ ልምድ መቅሰም መቻሉን አቶ ጌትነት አስታውቀዋል፡፡

መምህር ዳንኤል መኮንን በትምህርት ቤቱ የሒሳብ ትምህርት መምህር ሲሆኑ ትምህርት ቤቱ አጭር የጽሁፍ ማስተላለፊያ መስመሩን መጠቀም መጀመሩ ከመምህራንም ሆነ ከሌሎች የአስተዳደር ሰራተኞች ጋር ባሉበት በቀላሉ መገናኘት እንዳስቻለው ሲገልጹ ተማሪ ዮርዳኖስ ገብረኪዳን በበኩላ  ቀደም ሲል ከትምህርት ቤት ለወላጆቻቸው የሚላኩ መልዕክቶች በወረቀት እንደነበሩ ገልጻ አሁን ግን በአጭር የጽሁፍ መላኪያ ቁጥሩ በቀላሉ መገናቸት መቻሉን ጠቁማለች ፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

 ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 22/10/2014 ዓ.ም

የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በዩኒቨርስቲዎች ዉስጥ እንደሚሰጥ ተገለፀ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ  በሆሳዕና ፣ በወራቤና በወልቂጤ ከተሞች የሚገኙ  ሁለተኛ ደረጃና ሞዴል ትምህርት  ቤቶችን  ጎብኝተዋል።

በጉብኚታቸዉ ወቅት ከተማሪዎችና ከትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ ጋር ባደረጉት ቆይታ የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና በትምህርት ቤቶች ሳይሆን በዩኒቨርስቲ ውስጥ  እንደሚሰጥ ገልጸዋል።

እንደሚኒስትሩ ገለጻ የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና በኤሌክትሮኒክስ /online/ መስጠት እስከሚጀመር ድረስ  በዩኒቨርስቲዎች መሰጠቱ ይቀጥላል ።

የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና በዩኒቨርስቲ እንዲሰጥ የተወሰነው የፈተና ሰርቆትና ማጭበርበርን ለማስቀረት ታስቦ  በመሆኑ ተማሪዎች ትምህርት በስራና በታታሪነት የሚገኝ መሆኑን አውቀው በርትተው መማር ፣ማጥናትና ማወቅ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

የትምህርት ሚኒስቴር የትምህርትን ጥራትን ለማሻሻል በአጠቃላይና ከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፎች ሌሎችንም የተለያዩ እርምጃዎች በመውሰድ ላይ መሆኑንም ፕሮፌሰር ብርሀኑ መጠቆማቸዉን ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነዉ መረጃ ያሳያል ።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

 ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 22/10/2014 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2014 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና አፈጻጸም ዙሪያ ሂደቱን ለመከታተል ከተቋቋመው የኮማንድ ፖስት አደረጃጀት ጋር ውይይት አካሄደ ፡፡

በውይይቱ የከተማ አስተዳደሩና የክፍለ ከተማ የሰላምና የጸጥታ እንዲሁም የፖሊስ ኮሚሽን አመራሮችን ጨምሮ የክፍለ ከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊዎች ተሳታፊ የሆኑ ሲሆን ፈተናው ዘንድሮ ከሰኔ 27 እስከ 29/2014 ዓ.ም ድረስ ለተከታታይ ሶስት ቀናት እንደሚሰጥ የወጣው መርሀ ግብር  ያሳያል፡፡

የአዲስ  አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ዘላለም ሙላቱ የፈተና አፈጻጸም ሂደቱን አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ ፈተናው ሰላማዊ ሆኖ በስኬት እንዲጠናቀቅ ከፈተና ህትመት ጀምሮ የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መሰራታቸውን ገልጸው በከተማ አስተዳደሩ በሁሉም የመፈተኛ ጣቢያዎች የፈተና ሂደቱ ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ እስከ ፍጻሜው ድረስ ያለምንም የጸጥታ ችግር እንዲጠናቀቅ የትምህርት መዋቅሩ እንደተለመደው ከፖሊስም ሆነ ሌሎች ጉዳዩ ከሚመለከታቸው የጸጥታ ሀይሎች ጋር በጋራ እንደሚሰራ አስታውቀዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዲናኦል ጫላ በበኩላቸው በ2014 ዓ.ም በከተማ አስተዳደሩ በ179 የመፈተኛ ጣቢያዎች 71,832 ተማሪዎች ፈተናውን እንደሚወስዱና ለሁሉም ተማሪዎች አድሚሽን ካርድ መታደሉን ጠቅሰው በፈተናው ወቅት ከጣቢያ ኃላፊ ውጭ ማንኛውም አካል ሞባይል ይዞ ወደፈተና ጣቢያ መሄድ እንደማይችል በአጽንኦት አሳስበዋል፡፡

ዘንድሮ  በሁሉም የፈተና ጣቢያዎች 1,800 ፈታኝ ፤ 450 ሱፐር ቫይዘር ፤ 179 የፈተና ጣቢያ ኃላፊዎችን ጨምሮ በድምሩ 2,429 የፈተና አስፈጻሚዎች መመደባቸው የተገለጸ ሲሆን ከቢሮ ጀምሮ እስከ ፈተና ጣቢያዎች ድረስ የፈተናውን ሂደት የሚከታተል ኮማንድ ፖስት እንደተዋቀረም ተገልጻል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

 ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 21/10/2014 ዓ.ም

አሻራችን ለትውልዳችን!

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

 ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 21/10/2014 ዓ.ም

የከተማ አስተዳደሩ በዛሬው እለት አራተኛውን የአረንጓዴ አሻራ መረሀ ግብር በይፋ አስጀምሯል::

በአዲስ አበባ ከተማ አራተኛውን ዙር አረንጓዴ አሻራን በይፋ የማስጀመር መረሀ ግብር ላይ የኢፌዴሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ፣የኢፌዴሪ የግብርና ሚኒስቴር ሚንስትር አቶ ኡመር ሁሴን፣የኢፌዴሪ ሴቶች ሕጻናትና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚንስትር ዶክተር ኤርጓጌ ተስፋዬ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ አቶ ዘላለም ሙሉቱ እና ሌሎች ከፍተኛ የከተማ አስተዳደሩ የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች ፣ የሲቪክና ማህበራት ተወካዮች ፤ የሃይማኖት መሪዎች ፣ አርበኞች አርቲስቶች እና ተማሪዎች ተገኝተዋል፡፡

አረንጎዴ አሻራ የማስጀመሪያ መርሀ ግብር ላይ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንደተናገሩት በክቡር ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዐብይ አሕመድ አነሳሽነት የዛሬ አራት ዓመት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መረሀ ግብር በሀገር አቀፍ ደረጃ እንዲሁም በከተማችን በሚፈለገው ደረጃ ዘርፈ ብዙ ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል ብለዋል ።

ተፈጥሯዊም ሆነ የፖለቲካ ልዩነት ሳይገድበን ሀገራችንንም ሆነ ከተማችንን አረንጓዴ በማልበስ ለትውልድ የሚሻገር አሻራ በአንድነት እያኖርን እንቀጥላለን ያሉት ከንቲባ አዳነች በሁሉም ረገድ የሀገራችንን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ በቅንጅት መሥራት ይኖርብናል ብለዋል ። አክለዉም እኛ ልክ አንድ አንድ ልብ መካሪና ቃል ተናጋሪ ሆነን ችግሮቻችንን ከምንጫቸው በብልሀት እያደረቅን መትከላችንንና ልማታችንን አጠናክረን በማስቀጠል ለትውልድ በሁሉም ረገድ የተሻለች አገር እንገነባለን ሲሉ ተናግረዋል ።

መብላት እስካላቆምን ድረስ መትከልና መሥራት አናቆምም ያሉት ከንቲባ አዳነች አጠቃላይ የልማት ሥራዎቻችንን የምናከናውነው መጪውን ትውልድ ታሳቢ እያደረግን ብለዋል ።

በመጨረሻም ከንቲባ አዳነች ከሚያወራ የሚሰራ ፤ከሚያማ የሚያለማ ፤ከሚገፋ የሚያቅፍ ፤ከሚጠላ የሚወድ ከሚገድል የሚያድን ትውልድን የመገንባት አንዱ አካል ነው በማለት ገልፀዋል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

 ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 20/10/2014 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በክረምት እና በቅዳሜ እና እሁድ መርሀ ግብር 4,000 የቅድመ አንደኛ ደረጃ መምህራን ለቀጣይ ሶስት አመት ለማሰልጠን ከደብረ ብርሀንና አሰላ መምህራን ትምህርት ኮሌጆች ጋር የውል ስምምነት ተፈራረመ።

በመርሀ ግብሩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ዘላለም ሙላቱ፣ምክትል ቢሮ ኃላፊዎች፣የቢሮ አማካሪዎች፣ የደብረ ብርሀን መምህራን ትምህርት ኮሌጅ ዲን ረዳት ፕሮፌሰር መባ ፈጠነ፣የአሰላ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ ዲን ረዳት ፕሮፌሰር ጎሳ ግርማን ጨምሮ የአዲስ አበባ መምህራን ማህበር ስራ አስፈጻሚዎች እንዲሁም ሰልጣኝ መምህራኖችና ጉዳዩ የሚመለከታቸው ሌሎች የትምህርት ባለሙያዎች የተገኙ ሲሆን የደብረ ብርሀን መምህራን ትምህርት ኮሌጅ 2,500 መምህራንን በዲፕሎማ ለማሰልጠን እንዲሁም አሰላ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ 1,500 መምህራንን በዲፕሎማ ለማሰልጠን ውል ፈጽመዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ዘላለም ሙላቱ በመርሀ ግብሩ ባስተላለፉት መልዕክት የመምህራንን አቅም የማጎልበትና በተለያዩ ስልጠናዎች ማብቃት የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ዋነኛው ተግባር መሆኑን ገልጸው የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት የሚያስተምሩ መምህራን የትምህርት ደረጃቸውን ከሰርተፊኬት ወደ ዲፕሎማ ማሳደጋቸው በአዲሱ ስርአዓተ ትምህርት ለትምህርት እርከኑ የተቀመጠውን ስታንዳርድ ለማሟላት ከማገዙ ባሻገር በቅድመ አንደኛ ደረጃ ያለውን የመምህራን እጥረት ለመቅረፍ እንደሚረዳ አስታውቀዋል።

ኃላፊው አክለውም የትምህርት እድሉን ያገኙ ሰልጣኝ መምህራን ትምህርታቸውን በአግባቡ ተከታትለው በማጠናቀቅ ህጻናቱ ማግኘት የሚገባቸውን ዕውቀት ማስጨበጥ እንደሚጠበቅባቸው የአደራ መልዕክታቸውን ያስተላለፉ ሲሆን ኮሌጆቹም ቢሮው ያቀረበውን ጥያቄ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ተቀብለው ለመምህራኖቻችን እድሉን ስላመቻቹ ላቅ ያለ ምስጋና እንደሚገባቸው ጠቁመዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቴ ሳምሶን መለሰ በበኩላቸው የቅድመ አንደኛ ደረጃ መምህራኑ የዚህ እድል ተጠቃሚ መሆናቸው ህጻናቱ ጥራቱን የጠበቀና እድሜያቸውን ያማከለ ትምህርት እንዲያገኙ ከማስቻሉ ባሻገር ለአንደኛ ደረጃ ትምህርት ዝግጁ እንዲሆኑ እንደሚረዳቸው አስገንዝበዋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

 ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 19/10/2014 ዓ.ም

በልደታ ክፍለ ከተማ በወረዳ 2 ት/ጽ/ቤት ስር የሚገኘው ሰላም ቅድመ አንደኛ ት/ቤት136 የኬጂ 3 ተማሪዎችን በደማቅ ሁኔታ በዛሬዉ እለት አስመርቋል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

 ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 19/10/2014 ዓ.ም

የከተማ ግብርና በንፋስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች

የከተማ ግብርና በንፋስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በሚገኙት በመጋቢት 28፣ በቆጣሪ ፣በአብዮት ፋና እና በግንቦት 20 ትምህርት ቤቶች ያለበት ደረጃ ከፊል እይታ፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/  ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 11/10/2014 ዓ.ም

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አዘጋጅነት ከሰኔ 9 እስከ 11/2014 ዓ.ም የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ የብልጽግና ጉዟችንን በሳይንስ የፈጠራ ስራ እውን እናደርጋለን በሚል መሪ ቃል በድምቀት ሲካሄድ የቆየው ከተማ አቀፍ የሳይንስ ፈጠራ አውደ ርዕይ የመዝጊያ ስነ-ስርዓት በፎቶ።

በመርሀ ግብሩ ማጠቃለያ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ዘላለም ሙላቱ ባስተላለፉት መልዕክት ከተማ አቀፉ የሳይንስና ፈጠራ አውደ ርዕይ ከመክፈቻው ጀምሮ እስከ መዝጊያ ድረስ በደማቅና ስኬታማ ሆኖ እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋና አቅርበው የዘንድሮው አውደ ርዕይ ሌሎች መሰል መርሀ ግብሮችንም በድምቀት ማክበር እንደምንችል ያሳየ መሆኑን አስታውቀዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ አድማሱ ደቻሳ በበኩላቸው ላለፉት ሶስት ቀናት በድምቀት ሲካሄድ የቆየው ከተማ አቀፍ የሳይንስ ፈጠራ አውደ ርዕይ በሀገራችን በሳይንስና ቴክኖሎጂ  ዘርፍ ባለምጡቅ አእምሮ ትውልድ እየተፈጠረ እንደሚገኝ ያሳየ  መርሀ ግብር ከመሆኑ ባሻገር የሀገራችንን አንድነት የሚያጎለብቱ ትዕይንቶች የታዩበት መሆኑንም አስረድተዋል።

የመዝጊያ መርሀግብሩ የክብር እንግዳና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዮሀንስ ጫላ ባስተላለፉት መልዕክት በአውደ ርዕዩ  በተማሪዎችና መምህራን ተዘጋጅተው ለዕይታ የቀረቡት የሳይንስ ፈጠራ ስራዎች ሀገራችንን ወዳሰበችው የብልጽግና ጉዞ የማሸጋገር አቅም እንዳላቸው ገልጸው ቢሯቸው ከትምህርት ሴክተሩ ጋር በጋራ መስራቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስረድተዋል።

በመርሀ ግብሩ ማጠቃለያ በአውደ ርዕዩ በየትምህርት ደረጃው ውድድር በተደረገባቸው የፈጠራ ስራዎችና በሽብርቅ  አሸናፊ ለሆኑ ተማሪዎችና መምህራን እንዲሁም ክፍለከተሞች ሽልማት የተሰጠ ሲሆን ለመርሀ ግብሩ ስኬታማነት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የምስጋና ሰርተፍኬት ተበርክቶ ፕሮግራሙ ተጠናቋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

 ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

ቀን 11/10/2014 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ 7ኛዉ ከተማ አቀፍ የሳይንስና የፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ የመዝጊያ ስነ-ስርዓት መካሄድ ጀምራል።

የሳይንስና የፈጠራ ስራ አውደ ርዕዩ በከተማ ደረጃ ዘንድሮ ለ7ኛ ጊዜ ከሰኔ 9 እስከ 11/2014 ዓ.ም ድረስ “የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ የብልጽግና ጉዛችንን በሳይንስና ፈጠራ ዕውን እናደርጋለን!” በሚል መሪ ቃል በወዳጅነት አደባባይ ከፍተኛ የከተማ አስተዳደሩ የስራ ሀላፊዎች ፣ ተማሪዎች ፣ መምህራን ፣ የትምህርት ባለሙያዎች  እና አመራሮች በተገኙበት በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

 ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!