ቀን 10/5/2015 ዓ.ም

ለክርስትና ዕምነት ተከታዩች በሙሉ እንኳን ለጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ! 

የጥምቀት በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ ሀይማኖታዊ ትውፊቱን ጠብቆ በየዓመቱ በደማቅ ስነ-ስርዓት የሚከበር ክብረ በዓል ከመሆኑም ባሻገር ማህበራዊ ትስስርን የሚያጠናክር ማህበራዊ እሴት ነው፡፡ይህ ደግሞ ፍቅርን በማብዛት፣ ወንድማማችነትን በማሳደግ እና እርስ በእርስ መተዛዘንን በማጠናከር ለሀገር ግንባታ ትልቅ መሳሪያ ሆኖ ያገለግላል።

የጥምቀት በዓል በዩኔስኮ በማይዳሰሱ ቅርሶች በአለም ቅርስነት የተመዘገበ በአለም አደባባይ የምንታወቅበት ድንቅ ባህላችን ነው። በዓሉ የሀገራችን ብቻ ሳይሆን አለም በድምቀት የሚያከብረው የጋራ ኩራታችን የሆነ ታላቅ በዓላችን በመሆኑ ክብረ በዓሉ ሀይማኖታዊ ስርዓቱን ጠብቆ በሠላም እንዲጠናቀቅ ሁላችንም ኃላፊነታችንን መወጣት አለብን።

በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ ጥር 10 እና 11 ቀን የሚከበሩት የከተራ እና የጥምቀት በዓላት ከሃይማኖታዊ በዓልነት ባሻገር የሀገርን መልካም ገጽታን ከመገንባት እና የቱሪስት ፍሰትን ከማጎልበት አንጻር ጉልህ ሚና የሚጫወቱ በመሆኑ እንግዶችን በፍቅር ተቀብሎ በማስተናገድ በዓሉ በሰላም ተጀምሮ በሰላም እንዲጠናቀቅ ህብረተሰቡ በተለይም ደግሞ የትምህርት ባለድርሻ አካላት ከፀጥታ አካላት ጋር እጅና ጋንት በመሆኑ መስራት ይኖርባችዋል።

በመጨረሻም ለክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለአየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት በሰላም አደረሳችሁ!

በዓሉ የመተሳሰብ ፣ የመረዳዳት፣ የሰላም ፣ የፍቅር እና የጤና እንዲሆን እመኛለሁ፡፡

አመሰግናለሁ!

ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ ደሙ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s