ቀን 4/2/2015 ዓ.ም

የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤት በክፍለ ከተማው ከሚገኙ የመንግስትና የግል ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ተማሪዎችን በቅርቡ ግንባታው ተጠናቆ የተመረቀውን የሳይንስ ሙዚየም አስጎበኘ።

በጉብኝቱ ከተማሪዎች ባሻገር መምህራንና የትምህርት ባለሙያዎችን ጨምሮ ሱፐርቫይዘሮች ተሳታፊ መሆናቸውን የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሳምራዊት ቅባቱ ገልጸው በጉብኝቱ ተሳታፊ የሆኑ ተማሪዎች በሙዚየሙ የሚገ ኙ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ተመልክተው በቀጣይ በትምህርታቸው ታግዘው ተመሳሳይ የፈጠራ ስራዎችን መስራት እንዲችሉ እንደሚያግዛቸው አስረድተዋል።

ኃላፊዋ አክለውም የሳይንስ ሙዚየሙ ዘመኑ የደረሰበትን የቴክኖሎጂ ደረጃ የሚያሳዩ የተለያዩ የፈጠራ ስራዎች የሚገኙበት እንደመሆኑ በቀጣይም በሙዚየሙ ተመሳሳይ ጉብኝት በቀሪ ተማሪዎችና መምህራን እንደሚካሄድ አስታውቀዋል።

የሳይንስ ሙዚየሙን ለመጎብኘት እድሉን ያገኙ ተማሪዎችና መምህራን በበኩላቸው በሙዚየሙ የተመለከቷቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች ከፍተ ኛ አግራሞትን እና ተነሳሽነትን እንደፈጠሩባቸው ጠቁመው በሙዚየሙ  ጉብኝት እንዲያደርጉ እድሉን ላመቻቸላቸው የክፍለ ከተማው ትምህርት ጽህፈት ቤት ምስጋና አቅርበዋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s