የኢፌድሪ ጤና ሚኒስቴር ለተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።
የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፉን የጤና ሚኒስቴር ሚኒስተር ዶክተር ሊያ ታደሰ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ ለአቶ አድማሱ ደቻሳ አበርክተዋል።
በርክክብ መርሀ ግብሩ የኢፌድሪ ጤና ሚኒስቴር ዶክተር ሊያ ታደሰ ባስተላለፉት መልዕክት ሚኒስቴር መስሪያ ቤታቸው በስሩ የሚገኙ ተጠሪ ተቋማትን በማስተባበር የሰበሰባቸውን ደብተሮችን ጨምሮ እርሳሶችና እስክሪብቶዎችን 900 ለሚሆኑ ተማሪዎች በድጋፍ መልክ ማቅረቡን ገልጸው ድጋፉ የነገ ሀገር ተረካቢ ለሆኑ ተማሪዎች የተደረገ መሆኑ ከፍተኛ ደስታ እንደፈጠረባቸው አስታውቀዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ አድማሱ ደቻሳ በበኩላቸው የጤና ሚኒስቴር በከተማ አስተዳደሩ ለሚገኙ ተማሪዎች ላበረከተው የተለያዩ የመማሪያ ቁሳቁሶች ድጋፍ በትምህርት ቢሮና በተማሪዎች ስም ላቅ ያለ ምስጋና አቅርበው የጤናው ሴከተር ከትምህርት ሴክተሩ ጋር በተለያዩ ዘርፎች በጋራ የሚሰራ እንደመሆኑ በቀጣይ ቢሮው ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች በጋራ መስራቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስረድተዋል።
ሰላም ለኢትዮጵያውያን!
የኢትዮጵያ የሰላም አቋም ዘላቂና የማይናወጥ ነው!
የሰላማችን ዘብ ጀግናው ሰራዊታችን!
ሰላም ለሁለንተናዊ እድገታችን
እኔ የሰላም ዘብ ነኝ!
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ!’
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ!
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ!
ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!
You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ…
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/
Website: – aaceb.gov.et
Email;- aacaebc@gmail.com
Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/






