ቀን 2/7/2014 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተማሪ ወላጅ ማህበር (ተወማ ) የ2014 ዓ.ም የ6 ወር አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ።

በግምገማው የክፍለ ከተማ የማህበሩ ስራ አስፈጻሚዎችን ጨምሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የትምህርት ቤት መሻሻልና ሱፐር ቪዥን ዳይሬክቶሬት አመራሮችና ባለሙያዎች ተሳታፊ የሆኑ ሲሆን የተመረጡ ክፍለ ከተሞችና የከተማው የ6 ወር አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል።

በውይይቱ መክፈቻ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የትምህርት ቤት መሻሻልና ሱፐርቪዥን ዳይሬክቶሬት ተወካይ አቶ አብይ ተፈራ እንዳስታወቁት የተማሪ ወላጅ ማህበሩ በከተማ አስተዳደሩ በመማር ማስተማር ስራው ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማበርከት ላይ እንደሚገኝ ገልጸው በዚህ ውይይት ማህበሩ በየክፍለከተማውም ሆነ በከተማ ደረጃ ባከናወናቸው ተግባራት ላይ በመወያየት በቀጣይ ጊዜያት የተሻለ ስራ ለመስራት ጥረት ማድረግ እንደሚገባ አስረድተዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተማሪ ወላጅ ማህበር ሰብሳቢ ኢንጅነር ጌታቸው ሰጠኝ በበኩላቸው ማህበሩ ባለፉት 6 ወራት በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች የተለያዩ የድጋፍና ክትትል ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱንና በዚህም በአንዳንድ ትምህርት ቤቶች የሚስተዋሉ ችግሮችን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ በመሆን መፍትሄ እንዲያገኙ መስራቱን ገልጸው ማህበሩ ማከናወን የሚጠበቅበትን ተግባር በሚጠበቅበት ልክ ተግባራዊ ለማድረግ ያለበት የበጀት ውስንነት ችግር እንደፈጠረበትም አስገንዝበዋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s