ቀን 18 / 09 / 2012 ዓ/ም

የኮረና ቫይረስ ስርጭት መስፋፋትን ተከትሎ መንግስት ያስቀመጠውን የግል ትምህርት ቤቶች የክፍያ መመሪያ ተግባራዊ ለማድረግ ፍቃደኛ ያልሆኑ አራት ትምህርት ቤቶች ለአንድ አመት የእውቅና ፍቃዳቸው መታገዱን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ሙያ ብቃትና ምዘና ማረጋገጫ ባለስልጣን አስታወቀ፡፡

የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ሸዊት ሻንካ ጉዳዩን አስመልክተው ዛሬ በሰጡት መግለጫ አለም አቀፍ ወረርሽኝ የሆነው የኮረና ቫይረስ ስርጭት መስፋፋትን ተከትሎ የኢ.ፌ.ድ.ሪ. ትምህርት ሚኒስተር ከመጋቢት 7/2012 ዓ.ም ጀምሮ ትምህርት ቤቶች እንዲዘጉ በወሰነው መሰረት በከተማ አስተዳደሩ የሚገኙ  የግል ትምህርት ቤቶች የትምህርት አገልግሎታቸውን በተለያዩ መንገዶች እንዲሰጡና የሚያስከፍሉት የአገልግሎት ክፍያም ከ50 እስከ 75 ፐርሰንት እንዲሆን መወሰኑን ገልጸዋል፡፡

ወይዘሮ ሸዊት አክለውም ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ መመሪያው ተግባራዊ መሆኑን በትምህርት ቤቶቹ ክትትል ማድረጉንና አብዛኞቹ በወረደው መመሪያ መሰረት ተገቢውን ክፍያ በማስከፈል ላይ መሆናቸውን በመግለጽ 21 የሚሆኑ ትምህርት ቤቶች ከመመሪያው ውጪ ተገቢ ያልሆነ ክፍያ በመጠየቃቸው በአንድ ሳምንት ውስጥ ማስተካከያ እንዲያደርጉ በተሰጣቸው ማስጠንቀቂያ መሰረት 17 የሚሆኑት ማስተካከላቸውን ጠቁመው ቀሪዎቹ 4 ትምህርት ቤቶች ግን የክፍያ መመሪያውን ተግባራዊ ለማድረግ ፍቃደኛ ስላልሆኑ በ2013 ዓ.ም የትምህርት ዘመን አገልግሎት እንዳይሰጡ ለአንድ አመት እውቅና ፍቃዳቸው መታገዱን አስታውቀዋል፡፡

ፍቃዳቸው የታገደባቸው ትምህርት ቤቶች በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የሚገኙት ለምለም እና ሮማን ትምህርት ቤቶች እንዲሁም የካ ክፍለ ከተማ የሚገኘው ስሪ ኤም አካዳሚ ና አራዳ ክፍለ ከተማ የሚገኘው ገነት መሰረተ ክርስቶስ ትምህርት ቤቶች መሆናቸውን በመግለጫው ጠቅሰዋል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የዩቲዩብ ፣ የቴሌግራም ፣ የፊስቡክ እና የትዊተር ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

 Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Facebook : https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

እንራራቅ፣ እንታጠብ እንዲሁም አንጨባበጥ፡፡

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s