ቀን 26/6/2015 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የስርአተ ጾታ ማስረጽና ማካተት ዳይሬክቶሬት በተሻሻለው የስርአተ ጾታ መመሪያ እና ተዛማጅ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ በሁለት ዙር ሲሰጥ የነበረውን የአሰልጣ ኞች ስልጠና ማጠናቀቁን አስታወቀ።

በስልጠናው የክፍለ ከተማ የዘርፈ ብዙ ባለሙያዎችና ሱፐርቫይዘሮችን ጨምሮ ከተመረጡ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ የስነ ዜጋና ስነምግባር መምህራን፣የጋይዳንስና ካውንስሊንግ ባለሙያዎች እንዲሁም የመምህራን ማህበር ተወካዮች የተሳተፉ ሲሆን ሰልጣኞቹም የቀረቡ የመወያያ ርዕሰ ጉዳዮችን መሰረት በማድረግ በቡድን እና በጋራ ውይይት አካሂደዋል።

 የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የስርዓተ ጾታ ማስረጽና ማካተት  ባለሙያው አቶ ደረጀ ደምሴ በአሰልጣኞች ስልጠና መርሀግብሩ  በአዲስ መልክ ተሻሽሎ በተዘጋጀው  የስርአተ ጾታ ጥቃት መከላከያ መመሪያ ዙሪያ ሰልጣኞች በቂ ግንዛቤ ያገ ኙበትና በቀጣይ በየትምህርት ቤቶቻቸው መመሪያውን መሰረት በማድረግ ለትምህርት ማህበረሰቡ ተገቢውን ግንዛቤ መፍጠር የሚያስችላቸውን ስራ መስራት እንዲችሉ የሚያግዛቸው መሆኑን ጠቁመው በተያያዘ በዚህ ዘመን በርካታ ታዳጊ ወጣቶች ሰለባ እየሆኑበት ባለው ከማህበራዊ ሚዲያ ጋር በተገናኘ በሚከሰቱ ጥቃቶች ዙሪያ በዘርፉ ልምድ ባላቸው ባለሙያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መሰጠቱን አስረድተዋል።

በስልጠናው ኬኒያዊቱዋ የዩኒሴፍ ኢትዮጵያ የህጻናት የማህበራዊ ሚዲያ ጥቃት መከላከል አማካሪዋ ሚስ ቤትሪስ ጋቼንጎ ከታዳጊ ህጻናት የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ጋር በተገናኘ የሚታዩ አዎንታዊ እና አሉታዊ ተጽእኖዎችን መሰረት ያደረገ ስልጠና የሰጡ ሲሆን ወላጆችም ሆኑ የትምህርት ባለድርሻ አካላት ታዳጊ ህጻናት የሚመለከቱዋቸው የማህበራዊ ሚዲያ መረጃዎች እድሜያቸውን ታሳቢ ያደረጉ እና ለተለያዩ ጎጂ ልማዶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ተገቢውን ክትትል ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።

በአሰልጣኞች ስልጠናው የተሳተፉ መምህራንም ሆኑ የትምህርት ባለሙያዎች ከስልጠናው ያገኙትን ግንዛቤ መሰረት በማድረግ በየትምህርት ቤቶቻቸው ያከናወኗቸው ተግባራት ምን ደረጃ ላይ እንደሚገኙ የድጋፍና ክትትል ስራ እንደሚሰራ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የስርአተ ጾታ ማስረጽና ማካተት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሯ ወይዘሮ አበባ ዘውዴ አስታውቀዋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

 Blog: – https://aacaebc.blogspot.com

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s