ቀን 20/6/2015 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የእቅድ በጀት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት የ2015 ዓ.ም የ6 ወር የቢ ኤስ ሲ እቅድ አፈጻጸም ምዘናን በዛሬው ዕለት ማካሄድ ጀመረ፡፡

ምዘናው እስከ 2014 ዓ.ም ድረስ በለውጥና መልካም አስተዳደር ዳይሬክቶሬት አማካይነነት ሲካሄድ ቆይቶ ዘንድሮ በእቅድ በጀት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት እንዲመራ በተወሰነው መሰረት ከትምህርት ቤት ጀምሮ እስከ ትምህርት ቢሮ ድረስ አስሩን ዋና ዋና ግቦች መነሻ በማድረግ የሚካሄድ ሲሆን  ቀደም ሲል ከ400 በላይ ለሚሆኑ መዛኞችና አስተባባሪዎች በምዘናው ሂደትና ለመመዘኛነት በተዘጋጁ መስፈርቶች ዙሪያ ኦረንቴስን መሰጠቱ  ይታወቃል፡፡ 

ምዘናው በዛሬው እለት በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተጀመረ መሆኑን እና ከነገ ጀምሮ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ የወረዳና ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤቶች እንደሚመዘኑ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የእቅድ በጀት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጌታሁን ለማ ገልጸው በትምህርት ተቋማት የሚካሄድ የቢ ኤስ ሲ እቅድ አፈጻጸም ምዘና ተቋማቱ ያሉበትን ደረጃ ለማወቅ ከማስቻሉ ባሻገር በተቋማቱ መካከል የውድድር መንፈስ በመፍጠር በቀጣይ የተሻለ ስራ ለመስራት  እንደሚያስችል አስታውቀዋል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

 Blog: – https://aacaebc.blogspot.com

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s