ቀን 15/6/2015 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የእቅድ በጀት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት የ2015 ዓ.ም የ6ወር የቢ ኤስ ሲ እቅድ አፈጻጸም ምዘና ለሚያካሂዱ መዛኞች ኦረንቴሽን ሰጠ፡፡

ምዘናው እስከ 2014 ዓ.ም ድረስ በለውጥና መልካም አስተዳደር ዳይሬክቶሬት አማካይነነት ሲካሄድ ቆይቶ ዘንድሮ የምዘና ስርዓቱ በእቅድ በጀት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት እንዲመራ በተወሰነው መሰረት ከትምህርት ቤት ጀምሮ እስከ ትምህርት ቢሮ ድረስ አስሩን ዋና ዋና ግቦች መነሻ በማድረግ አድርጎ የሚካሄድ ሲሆን  በኦረንቴሽኑ ከ400 በላይ መዛኞችና አስተባባሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ 

በትምህርት ተቋማት የሚካሄድ የቢ ኤስ ሲ እቅድ አፈጻጸም ምዘና ተቋማቱ ያሉበትን ደረጃ ለማወቅ ከማስቻሉ ባሻገር የውድድር መንፈስ በመፍጠር በቀጣይ የተሻለ ስራ መስራት እንደሚያስችል በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የእቅድ በጀት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሩ አቶ ጌታሁን ለማ ገልጸው በምዘና ሂደቱ በመዛኝነት የሚሳተፉ የትምህርት ባለሙያዎችም ሆኑ አመራሮች ለምዘናው የተዘጋጁ የመመዘኛ መስፈርቶችን መሰረት በማድረግ ምዘናውን ማካሄድ እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል፡፡

ምዘናው ከነገጀምሮ በሁሉም የመንግስት አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንዲሁም የወረዳና ክፍለከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤቶች ጨምሮ በአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ በሚገኙ የስራ ክፍሎች የሚካሄድ ሲሆን ተመዛኝ ተቋማትም መዛኞች ለምዘና በሚሄዱበት ወቅት ተገቢውን መረጃ በማቅረብ ለምዘና ስርአቱ ውጤታማነት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ማበርከት እንደሚጠበቅባቸው ዳይሬክተሩ አስረድተዋል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s