ቀን 6/6/2015 ዓ.ም

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ትምህርት እና የትምህርት ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ጉለሌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ ላይ ከትምህርት ተቋማት ባለቤቶች ጋር ውይይት አካሄዱ።

ጽህፈት ቤቶቹ በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት የብዝሃ ቋንቋ ስርዓት አተገባበር ዙሪያ ከግል የትምህርት ተቋማት ባለቤቶች ጋር የተወያዩ ሲሆን ከአፍ መፍቻ ቋንቋ በሁለተኛነት በሚሰጠው ተጨማሪ ቋንቋ የትምህርት አሰጣጥ ዙሪያ የጉለሌ ክፍ ለከተማ ትምህርት  ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ሚሊዮን ኮራ ገለጻ አድርገዋል፡፡

ከ7ኛ ክፍል ጀምሮ በሁሉም ትምህርት ቤቶች የአገር ውስጥ ቋንቋ መማራቸው እንደተጠበቀ ሆኖ ሁሉንም የትምህርት ዓይነቶችን በእንግሊዚኛ መማር እንዲችሉ መደረጉንም ገልጸዋል፡፡

የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ጉለሌ ቅርንጫፍ  ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ፍቅሩ ገቢሳ በአዲሱ የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ የትምህርት ጥራትን ከየትኛውም ጊዜ በላይ ማረጋገጥ እንደሚቻል አመላክተዋል፡፡

በውይይት መድረኩ ላይ የግል ትምህርት ቤቶች ባለቤቶች እንዲሁም የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተው ውይይት መካሄዱን ጉለሌ ኮሙኒኬሽን ዘግባል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s