ቀን 4/6/2015 ዓ.ም

ከ4ሺህ በላይ የትምህርት ባድርሻ አካላትን ያሳተፈ ስልጠና በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ እየተካሄደ ነው።

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ “በተደራጀ የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ የትምህርት ጥራትን እናረጋግጣለን” በሚል መነሻ  ፅሑፍ  በትምህርት ጥራት ዙሪያ 4,734 የመንግስትና የግል ትምህርት ተቋማት መምህራን፣ርዕሰ  መምህራን ፣የትምህርት ባለሙያዎች እንዲሁም አስተዳደር ሠራተኞች ተሳታፊ የሆኑበት ለሁለት ቀናት የሚቆይ ስልጠና እየሠጠ ይገኛል።

በዚህም ሀያ ሁለት የመንግስት ትምህርት ቤቶች ቡድኖችና በሀምሳ ሁለት የግል ትምህርት ቤቶች ቡድኖች በአጠቃላይ በሠባ አራት የቡድን ውይይቶች እየተካሄዱ እንደሚገኝም ተገልጿል።

በዚህ ስልጠና ላይ በትምህርት ጥራት ዙሪያ የባለድርሻ አካላት ሚና ምን መምሠል  እንዳለበት የሚጠቁም  ሰነድ የቀረበ ሲሆን በሰነዱም እንደ ሀገር በትምህርት ተደራሽነትና ጥራት የተሠሩ በርካታ ስራዎች ያሉ ጥንካሬዎችንና ድክመቶች ምን እንደሆኑ እና የከተማ አስተዳደሩ በመማር ማስተማር ሂደት ላይ ያሉ አንኳር ችግሮች ምን እንደሆ በሚጠቁሙ አጀንዳዎች ላይ ሰፊ ውይይቶችን እያካሄደ ነው።

ይህንን  የውይይት መድረክ በንግግር የከፈቱት የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሲሳይ ኬኔ እንዳሉት ለሠላም ያለንን ፍላጎት በትምህርት ጥራት ላይ በመድገም የትምህርት ባለድርሻ አካሉ በትውልድ ግንባታ ላይ ለሚደረገው እርብርብ የበኩሉን ኃላፊነት ሊወጣ ይገባልም ማለታቸዉን ለየሚ ኩራ ኮሚኒኬሽን ዘግባል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s