ቀን 1/6/2015 ዓ.ም

ሲ ኤም ኤ ሲ ጂ ኤም (CMA CGM) የተሰኘ ገብረሰናይ ድርጅት ግምታቸው አስር ሺ የአሜሪካ ዶላር የሚያወጡ የምግብ ማብሰያ ብረት ድስቶችን (ጎላዎች) ለትምህርት ቤቶች አበረከተ፡፡

የማብሰያ ብረት ድስቶቹ መጠናቸው ከፍተኛ ከመሆኑ ባሻገር ብዘታቸው 42 ሲሆን በዋናነትም በየትምህርትቤቶቹ ያለውን የተማሪዎች የምገባ አገልግሎት እንዲያግዙ በማሰብ ድጋፍ መደረጉን በዛሬው እለት ከመጋቢ እናቶች ጋር ርክክብ በተደረገበት ወቅት ተገልጻል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ድጋፉን ከግብረሰናይ ድርጅቱ ተወካዮች በተረከቡበት ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርት ቤቶች የምገባ አገልግሎት ከተጀመረ ጊዜ አንስቶ ተማሪዎች ሙሉ ትኩረታቸው በትምህርታቸው ላይ እንዲሆን ከማስቻሉ ባሻገር ለወላጆች እፎይታ መስጠቱን እና ለበርካታ መጋቢ እናቶች ደግሞ የስራ እድል መፍጠሩን ጠቁመው ሲ ኤም ኤ  ሲ ጂ ኤም (CMA CGM) የተሰኘ ገብረሰናይ ድርጅት ለምገባ አገልግሎቱ የሚውሉ እነዚህን የመሰሉ ድጋፎች በማድረጉ በቢሮውና በተመጋቢ ተማሪዎች ስም ምስጋና አቅርበው ድርጅቱ በቀጣይም ተመሳሳይ ድጋፍ ማድረጉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል  እምነታቸው መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

የሲ ኤም ኤ ሲ ጂ ኤም(CMA CGM) ገብረሰናይ ድርጅት የኢትዮጵያ ስራአስካሄጅ አቶ ሀይሉ ተስፉ በበኩላቸው ድርጅቱ መቀመጫውን ፈረንሳይ ሀገር በማድረግ በኢትዮጵያ የተለያዩ ተግባራትን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ገልጸው በአዲስ አበባ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ላለው የተማሪዎች የምገባ አገልግሎት ድጋፍ የሚውሉ የብረት ድስቶች በመጋቢ እናቶች አማካኝነት በማቅረቡ ከፍተኛ ደስታ እንደሚሰማቸውን በትውልድ ግንባታ ሂደቱ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት መወጣታቸውን በመጥቀስ ድርጅታቸው በቀጣይም ከትምህርት ሴክተሩ ጋር በጋራ እንሚሰራ አስረድተዋል፡፡ 

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s