ቀን 29/5/2015 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የስርዓተ ጾታ ማስረጽና ማካተት ዳይሬክቶሬት ለቢሮው ሴት ሰራተኞች ለሁለት ቀን የሚቆይ ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡

በስልጠናው የትምህርት ዝግጅታቸው የመጀመሪያ ዲግሪ እና ከዛ በላይ የሆኑ የቢሮው ሴት ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን ስልጠናውም በዋናነት ሴቶችን ወደ አመራርነት ለማምጣት የሚያስችሉ ጽንሰ ሀሳቦችን መሰረት አድርጎ የተዘጋጀ ነው፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የስርአተ ፆታ ማስረጽና ማካጸጽ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወይዘሮ አበባ ዘውዴ በስልጠናው መክፈቻ ባስተላለፉት መልዕክት የመስሪያቤታችን  ሴት ባለሙያዎች ወደ ተለያዩ  የአመራርነት ቦታዎች ለመምጣት ራሳቸውን በትምህርትም ሆነ ለአመራርነት ብቁ በሚያደርጉ ስልጠናዎች ማብቃት እንደሚጠበቅባቸው ጠቁመው በትምህርት ሴክተሩ የሴቶች የአመራርነት ድርሻ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን እና በዚህ ሂደትም በሴቶች የሚመሩ ትምህርት ቤቶች አበረታች ውጤት በማስመዝገብ ላይ እንደሚገኙ አስታውቀዋል፡፡

ስልጠናውን ከከፍታ ለመድረስ የማህበረሰብና የተቃማት ስብእና ግንባታ ማዕከል የመጡት አቶ ዘላለም ይትባረክ ሴቶችን ወደ አመራርነት ማምጣት በሚል ርዕስ ያዘጋጁትን የስልጠና ሰነድ  መሰረት አድርገው የሰጡ ሲሆን ሰልጣኞቹም በስልጠናው የሚነሱ ጉዳዮችን መሰረት በማድረግ በቡድን እና በጋራ በመሆን  ውይይት እንደሚያደርጉ ከስልጠናው አስተባባሪዎች ያገኘነው መረጃ ያሳያል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s