ቀን 28/5/2015 ዓ.ም

ኮከበ ጽበሀ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተመሰረተበትን 90ኛ አመት በድምቀት አከበረ።

በክብረ በአሉ የትምህርት ቤቱ የቀድሞ ተማሪዎችን ጨምሮ መምህራን ወልጆች ተማሪዎችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የተገኙ ሲሆን በዝግጅቱ የትምህርት ቤቱን የእስካሁን ጉዞ የሚያሳይ የፎቶግራፍ አውደ ርዕይ ከመቅረቡ ባሻገር ትምህርት ቤቱ ያስገነባው የህጻናት ማቆያ /day care/ተመርቋል።

የኮከበ ጽበሀ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር አቶ ካሳሁን መኮንን በክብረ በአሉ መክፈቻ እንደገለጹት ትምህርት ቤቱ በ19 24 ዓ.ም ቀዳማዊ ሀይለ ስላሴ (ቀሀስ) ትምህርት ቤት በሚል ስያሜ ተከፍቶ የመማር ማስተማር ስራውን ሲያካሂድ ቆይቶ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ አሁን የሚጠራበትን ስያሜ በመያዝ ላለፉት አመታት ለበርካታ ተማሪዎች የትምህርት አገልግሎት ሲሰጥ መቆየቱን ገልጸው በዚህም አያሌ የቀድሞ የትምህርት ቤቱ ተማሪዎች በተለያዩ ከፍተኛ ቦታዎች ደርሰው  ሀገራቸውንና ህዝባቸውን በማገልገል ላይ እንደሚገኙ አስረድተዋል።

የመርሀ ግብሩ የክብር እንግዳና የየካ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤት ተወካይ አቶ አንተነህ ዮሴፍ በበኩላቸው ትምህርት ቤቱ 90ኛ የምስረታ አመቱን በማክበሩ ለትምህርት ቤቱ ማህበረሰብና ለቀድሞ ተማሪዎች እንኳን አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልጸው ኮከበ ጽበሀ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በሀገራችን የትምህርት አገልግሎት መስጠት ከጀመሩ ቀደምት ትምህርት ቤቶች መካከል አንዱ መሆኑን እና ለሀገራችን የትምህርት ስርአት መሰረት የጣለ አንጋፋ ትምህርት ቤት መሆኑንም አስገንዝበዋል።

በዝግጅቱ የቀድሞ የትምህርት ቤቱ ተማሪዎች ንግግር ከማድረጋቸው ባሻገር በአሁኑ ወቅት በትምህርት ቤቱ የሚማሩ ተማሪዎች የተለያዩ የኪነጥበብ ስራዎችን አቅርበው የክብረ በአሉን ታዳሚዎች አዝናንተዋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s