ቀን 27/4/2015 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በአዲሱ የተቋሙ አዳረጃጀት መመሪያ ዙሪያ ላይ ለሰራተኞች ኦረንቴሽን ሰጠ።

ኦረንቴሽኑ መዋቅሩን ባጠኑ ኮሚቴዎች የተሰጠ ሲሆን አደረጃጀቱም አዋጅ ቁጥር 74/2014 መሰረት አድርጎ መዘጋጀቱን በኮሚቴዎች ከመገለጹ ባሻገር መዋቅሩም በፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ ጸድቆ መምጣቱ ተጠቁሟል።

በመርሀ ግብሩ መክፈቻ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሲሳይ እንዳለ እንዳስታወቁት መዋቅሩ ለውጡን ተከትሎ ከተማ አስተዳደሩ ለህዝቡ የሚሰጠውን አገልግሎት ቀልጣፋና ውጤታማ እንዲሆን በማሰብ በአዲስ መልክ እንዲጠና መደረጉን ገልጸው የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮም በየደረጃው የሚሰጠውን አገልግሎት ውጤታማ ማድረግ እንዲችል የሚረዳ አደረጃጀት ልምድ ባላቸው የትምህርት ባለሙያዎች ማስጠናቱን አስረድተዋል።

የጽህፈት ቤት ኃላፊው አክለውም ቢሮው ጥናቱን በሚፈልገውና አጥኚ ቡድኑ ባጠናው መሰረት አዳዲስ የስራ ክፍሎችን በማደራጀት ማጸደቁን ጠቁመው የቢሮው ባለሙያዎችም በመመሪያው መሰረት ስራልምዳቸውም ሆነ የትምህርት ዝግጅታቸው በሚጋብዛቸው መደብ መወዳደር እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s