ቀን 14/4/2015 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የስርአተ ጾታ ማስረጽና ማካተት ዳይሬክቶሬት የፀረ ጾታዊ ጥቃት ጥቃት ቀን ወይም የነጭ ሪቫን ቀንን የቢሮው ሰራተኞት በተገኙበት አከበረ።

ቀኑ ዘንድሮ ሴትን አከብራለሁ ጥቃቷንም እከላከላለሁ በሚል መሪ ቃል በአለም አቀፍ ደረጃ ለ31ኛ እንዲሁም በሀገራችን ደግሞ ለ17ኛ ጊዜ ከህዳር 16 ጀምሮ በተለያዩ መርሀ ግብሮች ሲከበር መቆየቱ ተገልጿል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሲሳይ እንዳለ በመርሀ ግብሩ ባስተላለፉት መልዕክት ቀኑ ሴቶች ላይ የሚደርስን ጥቃት ለመከላከል በማሰብ በተለይም በወንዶች የሚከበር እንደመሆኑ በሴቶች ላይ የሚደርስ ማን ኛውንም ጥቃት በመከላከል የሀገርን ሁለንተናዊ እድገት ማስቀጠል እንደሚገባ ጠቁመው የትምህርት ማህበረሰቡም ሆነ ጉዳዩ የሚመለከተው ማን ኛው ባለድርሻ አካል በትምህርት ተቋማት የሚስተዋሉ ጾታዊ ጥቃቶችን ለመከላከል በሚደረገው እንቅስቃሴ የበኩላቸውን ኃላፊነት መወጣት እንደሚጠበቅባቸው አስረድተዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የስርአተ ጾታ ማስረጽና ማካተት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወይዘሮ አበባ ዘውዴ በበኩላቸው የነጭ ሪቫን ቀን እ.አ.አ ታህሳስ 1989 ዓ.ም ካናዳ ሞንትሪያል ከተማ በአንድ ወጣት ወንድ 14 ሴት ተማሪዎችን አስከፊ በሆነ መልኩ መገደላቸውን መሰረት በማድረግ እ.አ.አ ከ19 91ዓ.ም ጀምሮ ወንዶች ሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን በመቃወም የሚከበር መሆኑን ገልጸው ጾታዊ ጥቃትን ከመከላከል አንጻር የወንዶች ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ጥቃቱን ማውገዝና መከላከል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

በመርሀ ግብሩ ማጠቃለያ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳኘው ገብሩ ባስተላለፉት መልዕክት ቀኑ ሴቶች ላይ የሚደርስ ማንኛውንም ጥቃት ከአስተሳሰብ ጀምሮ በማውገዝና በመከላከል ተግባራዊ እንቅስቃሴ ማድረግ እንደሚገባ አስታውቀዋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ…

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s