ቀን 4/4/2015 ዓ.ም

በአዲስ አበባ ከተማ ባሉ ክፍለ ከተሞች በዛሬው ዕለት ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ከተወጣጡ ነዋሪዎች ጋር በወቅታዊ ከተማዊ ጉዳይ ላይ ውይይት ተካሄደ።

ትኩረቱን የትምህርት ቤቶችን ሰላማዊ መማር ማስተማር ዙሪያ ያደረገው የውይይት መድረክ የትምህርት ተቋማትን መጠበቅና የተጣለባቸውን ተልእኮ እንዲወጡ ለማድረግ ህብረተሰቡ ኃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት የተገለጸ ሲሆን ትምህርት ቤቶች በትምህርት ላይ ብቻ እንዲያተኩሩ ማድረግ እንደሚገባና ተቋማቱንና ተማሪዎችን ለሌላ ተልዕኮ መጠቀሚያ የሚያደርጉ አካላትንም መከላከልና አሥፈላጊውን እርምጃ መውሰድ እንደሚገባ ተነሥቷል።

በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ በውይይት መድረኩ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ የህዝብ ግንኙነት አማካሪ አቶ አለማየሁ እጅጉ፤ ሌላ የፖለቲካ አጀንዳ ያላቸው አካላት ሀገራዊ የልማትና ሠላም መሥፈንን ለማደናቀፍ በተለይም ትምህርት ቤቶቹን መጠቀሚያ ለማድረግ መሞከራቸውን ገልጸዋል።

ይሁን እንጂ የከተማ አሥተዳደሩ ከነዋሪው ጋር በመሆን ችግር በሚፈጥሩ አካላት ላይ አስፈላጊውን እርምጃ እንደሚወስድና የሚወድም ንብረትም የህዝብ በመሆኑ ማህበረሠቡ መጠበቅ እንደሚገባው አቶ አለማየሁ አሳስበዋል።

የውይይቱ ተሣታፊዎችም ወላጆች ልጆቻቸውን ከመቆጣጠር ጀምሮ ተቋማቱን በመጠበቅና ችግር የሚፈጥሩ አካላትን በማጋለጥ ከመንግሥት ጋር በትብብር መሥራት እንደሚገባ መጠቆማቸውን ሜር ኦፊስ ዘግባል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s