ቀን 6/3/2015 ዓ.ም

የፓናል ውይይት ለሚያወያዩ አስልጣኞች የአስልጣኞች ስልጠና ተሰጠ፡፡

በአስልጣኞች ስልጠና መድረክ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ አማካሪ የሆኑት ወ/ሮ አበበች ነጋሽ በሀገራችን ‘’ህብረብሄራዊ አንድነታችን ለዘላቂ ሰላማችን!’’ በሚል መሪ ቃል ዘንድሮ ለ17 ጊዜ  የሚከበረው የኢትዮጵያ ብሄሮች ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በአዲስ አበባ በሁሉም የትምርት መዋቅር መለትም በቢሮ ፣ በክፍለ ከተማ ፣ በወረዳ እና በትምህርት ቤት ደረጃ በተማሪዎች የጥያቄና መልስ ውድድሮች ፣ በፓናል ውይይቶች እና ህብረብሄራዊነትን በሚያሳዩ ትዕይንቶች የሚከበር መሆኑ ጠቅሰዋል፡፡

ሀላፊዋ አክለውም የአስልጣኞች ስልጠና መስጠት ያስፈለገበትን ምክንያት ሲገልጹ በየደረጃው የሚደረገው የፓናል ውይይት በሀገር አቀፍ ደረጃ የተዘጋጀ በመሆኑ ዛሬ በስልጠናው ላይ የተሳተፉ አካላት መጨበጥ የሚገባቸውን ዋና ዋና ነጥቦች እንዲይዙ እና በቀጣይ በየደረጃው ለሚደረጉ የፓናል ውይይት አወያዮች ተመሳሳይ ግንዛቤ እንዲጨብጡ ለማድረግ ታስቦ የተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አማካሪ አቶ ጥላሁን ፍቃዱ በበኩላቸው በሀገራችን ሰላም እንዲረጋገጥ  በጋራ ተግባብቶና ተናቦ መስራ እንደሚያስፈልግ ገልጸው ህብረብሄራዊነታችን ለአንድነታችን መረጋገጫ እና ለሰላማችን መበልጸግ የሚኖረው ሚና የጎላ በመሆኑ ስልጣኞች የሚሰጣቸውን ስልጠና በመውሰድ የታለመው ግብ እዲሳካ መስራት ይገባል ብለዋል፡፡    

በአስልጣኞች ስልጠና መድረኩ ስልጠናው በአቶ ዘሪሁን አለማየሁ የተሰጠ ሲሆን ከ11ዱም ክፍለ ከተማዎች የተውጣጡ ባለሙያች እና መምህራን ተሳታፊ ሆነዋል፡፡  

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s