ቀን 6/3/2015 ዓ.ም

“ህብረ ብሔራዊ አንድነታችን ለዘላቂ ሰላማችን” በሚል መሪ ቃል ለ17ኛ ጊዜ የሚከበረውን የ2015 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሄሮች ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀንን በማስመልከት በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ የተማሪዎች ጥያቄና መልስ ውድድር ተካሄደ፡፡

በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ውስጥ በሚገኙ 1ኛና 2ኛ ደረጃ የመንግስትና የግል ት/ቤት ተማሪዎች ለ17ኛ ጊዜ የሚከበረውን የኢትዮጵያ ብሄሮች ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓልን በየት/ቤቶች በተለያዩ ዝግጅቶች በደመቀ ሁኔታ እየተከበረ መሆኑና ከበዓሉ አከባበር አንዱ የሆነው በክፍለ ከተማው ትምህርት ጽ/ቤት አዘጋጅነት የተካሄደው የተማሪዎች የጥያቄና መልስ ውድድር ሲሆን ብርቱ ፉክክር የተደረገበት መሆኑን እና በቀጣይ ተማሪዎች በሀገርና በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ  እንዲሆን ለማድረግ እንደሚያግዝ የክፍለ ከተማው ትምርት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሪት ሳምራዊት ቅባቱ ገልጸዋል፡፡

ሃላፊዋ አክለውም በስነ-ምግባራቸው ተማሪዎች የተመሰገኑ፣ ውጤታማ እና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ በፕሮግራሙ ላይ ለተገኙ ተማሪዎች መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

በአቢሲኒያ ሁለተኛ ደረጃና በእድገት አንደኛ ደረጃ ት/ቤቶች በተካሄደው የጥያቄና መልስ ውድድር ለአሸናፊ ተማሪዎችና ት/ቤቶች የማበረታቻ ሽልማት መበርከቱን ከክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያሳያል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s