ቀን 12/2/2015 ዓ.ም

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ለመፈተን ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የመጡ የፈተና አስፈጻሚዎችን በከተማው የሚገኙ ታላላቅ ፕሮጀክቶችን አስጎበኘ።

ጉብኝቱ በዋናነት በእንጦጦና አንድነት ፓርክን ጨምሮ በወዳጅነት አደባባይና በቅርቡ ለዕይታ በበቃው የሳይንስ ሙዚየም የተካሄደ ሲሆን በጉብኝቱ 1200 የሚሆኑ የፈተና ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳኘው ገብሩ በጉብኝት መርሀ ግብሩ ባስተላለፉት መልዕክት በከተማ አስተዳደሩ ፈተናው በተሰጠባቸው 9 የፈተና ጣቢያዎች ፈተናው ያለምንም እንከን እንዲጠናቀቅ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ለተወጡ ፈታኞች ምስጋና አቅርበው ከተማ አስተዳደሩ በትምህርት ቢሮ አማካይነት የሸገር ማስዋብ አካል የሆኑ ትላልቅ ፕሮጀክቶችን የፈተና አስፈጻሚዎች እንዲጎበኙ በማድረጉ ከፍተኛ ደስታ እንደሚሰማው አስታውቀዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሩ አቶ ዲናኦል ጫላ በበኩላቸው ቢሮው የፈተና አስፈጻሚዎቹን በከተማው የሚገኙና የቱሪስት መዳረሻ የሆኑ ፕሮጀክቶችን ከማስጎብኘቱ ባሻገር ፈተና አስፈጻሚዎቹ በአዲስ አበባ ቆይታቸው ፈተናውን ያለምንም ችግር እንዲያስፈጽሙ የመኝታና የምግብ አገልግሎት ሲሰጥ መቆየቱን ጠቅሰው ፈተና አስፈጻሚዎቹም ከአቀባበል ጀምሮ በተደረገላቸው መስተንግዶ ለከተማ አስተዳደሩ እና ለትምህርት ቢሮ ምስጋና ማቅረባቸውን አስረድተዋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s