ቀን 7/12/2014 ዓ.ም

የቦሌ ክፍለከተማ አስተዳደር በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ308 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው 47 ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ማድረጉን አስታወቀ፡፡

አሰሰተዳደሩ  በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 22 የ60 ቀናት ፕሮጀክቶችን ጨምሮ  የትምህርት ፣ የጤና ፣ የስፖርት እና ሌሎችም ማሕበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ፕሮጀክቶችን እንዳጠናቀቀ የክ/ከተማው የዲዛይንና ግንባታ ፅ/ቤት ኃላፊ ኢ/ር አባይነህ ባጫ ገልፀዋል፡፡

በጊዜ ማዕቀፉ ፅ/ቤቱ ግንባታቸውን አጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ካደረጋቸው ፕሮጀክቶች መካከል

  • መገኛው ወረዳ 13 የሆነውና  ከ14 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የወሰደው የቦሌ ሕብረተሰብ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት G+4 ህንፃ፤
  • የውለታ መጠኑ ከ5 ሚሊዮን ብር በላይ የሆነው የወረዳ 10 መሪ ትምህርት ቤት 3*1 ሜዳ፤
  • በወረዳ 09 ውስጥ በብቸኝነት የሚገኘውና 30 ክፍሎች እንዲኖሩት ተደርጎ ከ19 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ  የተገነባው የምስራቅ በር ቁጥር 2 አፀደ ሕፃናት፤
  • 13 ሚሊዮን ብር የወጣበት ወረዳ 09 ጎሮ G +2 ቤተ-መፅሐፍት ጥቂቶቹ ሲሆኑ ሌሎችም ሰፊ ማሕበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያላቸው በርካታ ፕሮጀክቶች በፅ/ቤቱ ባለቤትነት ተገንብተው ለአገልግሎት ዝግጁ መደረጋቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡

ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!

ሀገርን በዘላቂነት እናልማ!

የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ!

ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ!

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s