ቀን 29 /11/2014 ዓ.ም

የሬዲዮ ትምህርት ስክሪፕት ዝግጅት ተጀመረ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሰረት ለተማሪዎች ድጋፍ የሚያደርጉ የሬዲዮ ትምህርቶችን ማዘጋጀት ላይ የሚገኝ ሲሆን ሂደቱም የሬዲዮ ትምህርት ስክሪፕት ዝግጅት ላይ መድረሱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ትምህርት ቴክኖሎጂ ልማት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ በለጠ ንጉሴ ገልጸዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የስርዓተ ትምህርት ዝግጅትና ትግበራ ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ጌታቸዉ ታለማ በበኩላቸዉ የሬዲዮ ትምህርት ይዘት መረጣ ተጠናቆ ወደ ስክሪፕት ጽሁፍ ዝግጅት ሂደት ላይ መደረሱን በማንሳት የሬዲዩ ትምህርት ስክሪፕት ዝግጅቱ እስከ ነሐሴ 14 ደረስ ቆይታ ያደርጋል ብለዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአፋን ኦሮሞ አጠቃላይ ስርዓተ ትምህርትና ሱፕርቪዥን ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ሮሚ ዋሚ በበኩላቸዉ በሁለቱም የአፍ መፍቻ ቋንቋዎች በመዘጋጀት ላይ የሚገኘዉ የሬዲዮ ትምህርት የስክሪፕት እንዴት ይዘጋጃል ፤ ምን ምን ርዕሰ ጉዳዮችን ያካታል በሚሉ ርዕሰ  ጉዳዮች ላይ ገለጻ በባለሙያዎች ከተሰጠ በሀላ ወደ ጽሁፍ ዝግጅቱ መገባቱን ተናግረዋል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s