ቀን 19/11/2014 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የለውጥና መልካም አስተዳደር ቡድን የ2014 በጀት አመት የትምህርት ተቋማት የቢ ኤስ ሲ ስኮር ካርድ እቅድ አፈጻጸም ምዘና በመካሄድ ላይ እንደሚገኝ አስታወቀ ።

ምዘናው ከትላንት ጀምሮ በሁሉም የመንግስት አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች፣ በክፍለ ከተማና ወረዳ ትምህርት ጽህፈት ቤቶች እንዲሁም በማዕከል ደረጃ በመካሄድ ላይ እንደሚገኝ የቢሮው የለውጥና መልካም አስተዳደር ቡድን መሪ ወይዘሮ እጸገነት አብዱ ገልጸው በሂደቱም 324 መዛኞችና 22 አስተባባሪዎች ተሳታፊ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

ቡድን መሪዋ አክለውም ምዘናው በስኬት እንዲጠናቀቅ ከመመዘኛ መስፈርት ዝግጅት ጀምሮ ለመዛኞችና አስተባባሪዎች ኦረንቴሽን ተሰጥቶ ወደ ምዘና መገባቱን ጠቁመው ምዘናው እስከ ሀምሌ 22/2014 ዓ.ም ድረስ እንደሚካሄድና የላቀ አፈጻጸም ያስመዘገቡ ተቋማት የምዘና ውጤቱን መሰረት በማድረግ እውቅና እንደሚሰጣቸው አስረድተዋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

Leave a comment