ቀን 18/11/2014 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አዲሱ ስርዓተ ትምህርትን መሰረት በማድረግ የሬዲዮ ትምህርት ይዘት መረጣ ማከናወን ጀመረ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አሰተዳደር ትምህርት ቢሮ ኤፍ ኤም 94.7 የትምህርት ሬዲዮ ጣቢያ በኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ተዘጋጅቶ እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የተተረጎመውን ስርዓተ ትምህርት መሰረት በማድረግ ለአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች እገዛ የሚያደርግ የሬዲዮ ትምህርት ዝግጅት የይዘት መረጣ በአማርኛ እና በአፋን ኦሮሞ ቋንቋዎች  ማድረግ መጀመሩን አሳወቀ፡፡ 

በመርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ አማካሪ  ወ/ሮ አበበች ነጋሽ  የአንደኛ ደረጃ  ትምህርት አዲሱ ስርዓተ ትምህርት ተዘጋጅቶ ወደ ሙከራ ትግበራ  ከገባ በሀላ በአሁኑ ሰሃት የመጻህፍት ህትመት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዉ ቢሮዉ ዝግጅቱን በከተማዉ መምህራን ፣ ባለሙያዎች እና የትምህርት አመራሮች አቅም እንዲከናወን ማድረጉ የሚመሰገን ተግባር መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ወ/ሮ አበበች  አክለውም በቀጣይ በ2015 ዓ.ም ወደ ሙሉ ትግበራ የሚገባ በመሆኑ ለሬዲዮ ትምህርት ዝግጅት ያግዝ ዘንድ የይዘት መረጣዉ ላይ ለመሳተፍ የተገኙ አካላት ውጤታማ ስራ እንዲሰሩ አደራ ብለዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አሰተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ትምህርት ቴክኖሎጂ ልማት እና ትግበራ ዳይሬክተር የሆኑት አቶ በለጠ ንጉሴ የትምህርት በሬዲዮ ዝግጅቱን አስመልክተዉ በሰጡት ማብራሪያ በመጀመሪያ ዙር የተዘጋጀዉ የአዲሱ ስርዓተ ትምህርት የሬዲዮ  ትምህርት  ይዘት መረጣ ሲጠናቀቅ ይዘት መረጣው  ምክረ ሀሳብ እንዲሰጥበት ከተደረገ በሃላ  ወደ ሙሉ የሬዲዮ ስክሪፕት ጽሁፍ ዝግጅት ሂደት የሚሻገር እና በቀጣይም  ወደ ድምጽ ቀረጻ ዝግጅት የሚገባ  መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አሰተዳደር ትምህርት ቢሮ ኤፍ ኤም 94.7 የትምህርት ሬዲዮ ጣቢያ ቡድን መሪ ወ/ሮ በላይነሽ የሻው በበኩላቸዉ በዝግጅቱ ላይ የሚሳተፉት ከአስራአንዱም ክፍለ ከተማ አዲሱን ስርዓተ ትምህርት በማዘጋጀት ላይ የተሳተፉ መምህራን፣ የስርዓተ ትምህርት ትግበራ ባለሙያዎች  እንዲሁም የሬዲዮ ፕሮግራም አዘጋጆች ናቸዉ ብለዋል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

 ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s