ቀን 28/10/2014 ዓ.ም

የዕድሜ ባለፀጋው የ8ኛ ክፍል ተፈታኝ፡፡

አባ ዘውገ ፈተናውን እየወሰዱ የሚገኘው በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 አስተዳደር በቃሊቲ ቅድመ መደበኛና የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ነው፡፡

አባ ዘውገ ትምህርታቸውን በማታዉ የትምህርት ክፍለ ጊዜ ሲከታተሉ ቆይተዋል፡፡

እኚህ አባት ሁሉም ሰው በዕድሜና በመሰል ጉዳዮች ሳይረታ ባገኘው አጋጣሚ መማር አለበት፤ እኔም ሞት ካልቀደመኝ እና ፈጣሪ ከረዳኝ እስከ ዩኒቨርሲቲ በመቀጠል በማገኘዉ ዕዉቀት ህዝቤን አገለግላለሁ ፈጣሪ ሀገራችንን እና ህዝቦቿን ይባርክ ብለዋል።

የወረዳው ትምህርት ጽኅፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢፋ አብሼ በበኩላቸው፥ “ትምህርት ዕድሜን አይገድብም ፤ ሁሉም ሰው ለመማር አዕምሮውን ዝግጁ ካደረገ የሚገድበው ነገር እንደሌለ እኚህ አባት ለዘመኑ ትዉልድ ትልቅ ማስተማሪያ ናቸው” ብለዋል፡፡

ትምህርት ተቀጥሮ ለመስራት ብቻ ሳይሆን ለኅሊና እርካታ ጭምር መሆኑንም የአባ ዘውገ ታሪክ ትልቅ ማስተማሪያ መሆኑን ነው ኃላፊው ያነሱት፡፡

የወረዳው ትምህርት ጽኅፈት ቤት ኃላፊው ለአባ ዘውገ መልካም የፈተና ጊዜ እና ጥሩ ውጤትም ተመኝተዋል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ…

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s