ቀን 27/10/2014 ዓ.ም

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተናን ማስጀመሩን አሳወቀ፡፡

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት በዛሬው እለት የከተማ አቀፍ የ8ኛ ክፍል ፈተና በክፍለ ከተማው ባሉ በሁሉም የመንግስት እና የግል የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ተቋማት ፈተናውን መስጠት መጀመሩን ገልጿል።

በክፍለ ከተማዉ የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በክፍለ ከተማ በሚገኙ አስራ ሥስት የመፈተኛ ጣቢዎች 7,404 ተማሪዎች ፈተናውን በዚህ ቀን መውሰድ መጀመራቸውንም ጨምሮ አሳውቋል።

በአሁን ሠዓት ፈተናው ፍፁም ሠላማዊ በሆነ መልኩ ተማሪዎቹ በተረጋጋ መንፈስ ፈተናውን መውሰድ መጀመራቸውን የትምህርት ጽ/ቤት የገለፀ ሲሆን ፈተናው ለሥስት ተከታታይ ቀናትም እንደሚቆይ ተጠቁሟል።

የ8ኛ ክፍል የከተማ አቀፍ ፈተናው ያስጀመሩት የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ባዩማ ወርቁ ለተማሪዎቹ ባስተላለፉት መልዕክት እናንተ የዛሬ ተማሪ የነገ የሀገር የተስፋ ብርሀን ናቹ ስለዚህ ትልቅ ራዕይ ሰንቃቹ የተሻለች እና ለሁሉ የምትሆን ሀገር በእናንተ ጊዜ እውን እድትሆን ይኸው ጉዞውን ዛሬ ጀምራቹዋል በማለት ለተማሪዎች መልካም ውጤትን ተመኝተዋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

 ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s