ቀን 24/10/2014 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት  በ2014 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ  ክልላዊ ፈተና  ላይ በድጋፍና ክትትል ተግባር ለሚሳተፉ የቢሮው ባለሙያዎች ኦረንቴሽን ሰጠ፡፡

በመርሀ ግብሩ የአዲስ  አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳኘው ገብሩ   ባስተላለፉት መልዕክት  ፈተናው ሰላማዊ ሆኖ በስኬት እንዲጠናቀቅ እና በፈተና ሂደቱ  የሚያጋጥሙ ችግሮች ቢኖሩ ከቢሮ የተመደቡ ባለሙያዎች መፍትሄ በመስጠት ፈተናው ያለምንም እንከን እንዲጠናቀቅ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዲናኦል ጫላ በበኩላቸው በ2014 ዓ.ም  በከተማ አስተዳደሩ በ179 የመፈተኛ ጣቢያዎች 71,832 ተማሪዎች ፈተናውን እንደሚወስዱ ጠቁመው በየፈተና ጣቢያዎቹ ለድጋፍና ክትትል የተመደቡ ባለሙያዎች የመልስ መስጫ ወረቀቱ በአግባቡ ተሰብስቦ መታሸጉን መከታተል እንደሚጠበቅባቸው አስረድተዋል፡፡

ዘንድሮ  ፈተናው ከሰኔ 27 እስከ ሰኔ 29/2014 ዓ.ም ድረስ የሚሰጥ ሲሆን  በሁሉም የፈተና ጣቢያዎች 1,800 ፈታኝ ፤450 ሱፐር ቫይዘር፤179 የፈተና ጣቢያ ኃላፊዎችን ጨምሮ በድምሩ 2,429 የፈተና አስፈጻሚዎች መመደባቸውን ከስራ ክፍሉ ያገኘነው መረጃ ያሳያል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

 ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s