ቀን 24/10/2014 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የስርአተ ጾታ ማስረጽና ማካተት ዳይሬክቶሬት የአፍሪካ ህጻናት ቀንን በኒው ኤራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አከበረ፡፡

በመርሀ ግብሩ ተማሪዎችና መምህራንን ጨምሮ ሌሎች የትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ አካላት ተሳታፊ የሆኑ ሲሆን ቀኑ ዘንድሮ በህጻናት ላይ የሚፈጸሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን በጋራ እንከላከል በሚል መሪ ቃል በአህጉራችን ለ32ኛ እንዲሁም በሀገራችን ለ31ኛ ጊዜ ታስቦ መዋሉን በመርሀግብሩ ተገልጻል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የስርአተ ጾታ ማስረጽና ማካተት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወይዘሮ አበባ ዘውዴ እለቱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት የአፍሪካ ህጻናት ቀን በ1976 ዓ.ም በደቡብ አፍሪካ ስዌቶ በወቅቱ በነበረው የአፓርታይድ ስርአት ሰልፍ በወጡ ተማሪዎች ላይ የፈጸመውን አስከፊ ጭፍጨፋ ለማሰብ እ.አ.አ በ1991 የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ባደረገው ስብሰባ በወሰነው መሰረት ቀኑ በመከበር ላይ እንደሚገኝ ገልጸው የጥቃቱ ሰለባዎች በዋናነት ህጻናት ተማሪዎች እንደመሆናቸው ቀኑ በትምህርት ቤቶች መታሰቡ ተማሪዎችን ከመሰል ጥቃት ለመከላከል እንደሚረዳ አስገንዝበዋል፡፡

በመርሀ ግብሩ የትምህርት ቤቱ ተማሪዎች እለቱን የተመለከቱ ግጥሞችና ድራማዎችን ጨምሮ የተለያዩ አስተማሪ ፕሮግራሞችን አቅርበዋል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

 ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s