ቀን 9/10/2014 ዓ.ም

7ኛዉ ከተማ አቀፍ የሳይንስና የፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ የመክፈቻ ስነ-ስርዓት በደማቅ ሁኔታ እንዲከናወን ላደረጉ አካላት የአዲሰ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ አቶ ዘላለም ሙላቱ ምስጋና አቀረቡ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ዛሬ በወዳጅነት ፓርክ ‘’ የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ የብልጽግና ጉዛችንን በሳይንስ ፈጠራ ስራ እውን እናደርጋለን! ” በሚል መሪ ቃል ለሶስት ቀናት ቆይታ የሚያደርግ የመምህራን እና የተማሪዎች የሳይንስና የፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ ደማቅ የመክፍቻ ስነ-ስርዓት አካሂዳል፡፡

በአውደ ርዕዩ ላይ የኢፌዴሪ እና የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ፣ መምህራን ፣ ተማሪዎች ፣ የትምህርት ባለድርሻ አካላት ፣ የትምህርት ባለሙያዎች እና አመራሮች ደምቀዉ ውለዋል፡፡

ተማሪዎች እና መምህራንም የፈጠራ ስራዎቻቸዉን ለማቅብ ችለዋል፡፡ የየክፍለ ከተማዉ ልዑካን ቡድኖችም ከዚህ ቀደም ከነበረዉ በላቀ እና በደመቀ ደረጃ አሽብርቀዉ እና ተውበዉ እለቱን አድምቀዋል፡፡ ይህንንም አስመልክት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ አቶ ዘላለም ሙላቱ የአውደ ርዕዩ የመክፈቻ መርሃ ግብር የተሳካ እንዲሆን ላደረጉ በየደረጃዉ ለሚገኙ የትምህርት አመራሮች ፣ ባለሙያዎች ፣ መምህራን ፣ ተማሪዎች ፣ ለጸጥታ እና ለሚደያ አካላት ለነበራቸዉ የላቀ አበርክቶ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

 ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s