ቀን 29/9/2014 ዓ.ም

የሚኪሊላንድ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት በንባብ ችሎታ ማሻሻል ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመረቀ።

የሚኪሊላንድ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ለሶስት ወራት ውስጥ እኔ በአጭር ጊዜ ውስጥ ማንበብ እችላለሁ! በሚል መሪ ቃል ያሰለጠናቸዉን ተማሪዎች ያስመረቀ ሲሆን መሰል ተግባራት የተማሪዎችን የማንበብ ክህሎት ለማዳበር የሚጫወቱት ሚና የጎላ መሆኑ በስነ-ስርዓቱ ላይ ተመላክቷል፡፡

በትምህርት ተቋሙ የሚያስተምሩ መምህራን የማንበብ ችግር ያለባቸዉን ተማሪዎች በመለየት እና በሶስት ወር ውስጥ ተማሪዎችን ካለማንበብ ወደ ማንበብ እንዲመጡ የተሰጠ ስልጠና መሆኑ እንዲሁም እኛ መምህራን እያለን በዚህ ትምህርት ቤት አንድም የማያነብ ተማሪ መኖር የለበትም በሚል አስተሳሰብ የተማሪዎችን የንባብ ከህሎት ለማሳደግ መቻሉ በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ ተገልጻል፡፡

በመርሃ ግብሩ የክፍለ ከተማዉ ትምህርት ጽ/ቤት ሀላፊ ወ/ት ሳምራዊት ቅባቱ በክብር እንግድነት በመገኘት መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ በተጨማሪም በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የአሀዱ ሬድዮ እና ቴሌቪዥን እንዲሁም የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች ማህበር  ፕሬዝዳንት አቶ ጥበቡ በለጠ ፣ ረዳት ፕሮፌሰር ደረጀ ገብሬ እንዲሁም በርከት ያሉ ታዋቂ ግለሰቦች ፣ ምሁራን እና የተመራቂ ተማሪ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

 ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s