ቀን 16/9/2014 ዓ.ም

“ተማሪዎች ዘንድሮ በያላችሁበት ትደግማላቸሁ” በሚል የሚናፈሰው ወሬ ከእውነት የራቀ ነዉ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ2014 የትምህርት ዘመን በከተማዉ የሚሰጠዉ ትምህርት ውጤታማ እንዲሆን ዘርፈ ብዙ ተግባራት በመከናወን ላይ የሚገኙ ሲሆን በዚህ ሂደት ውስጥ መምህራን ፣ ተማሪዎች ፣ ወላጆች ፣ የትምህርት ባለሙያዎች እና አመራሮች ፣ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ከምንጊዜውም በላይ የትምህርት ጥራት ፣ ተደራሽነት ፣ ተገቢነት እና ፍትሃዊነት እንዲረጋገጥ የበኩላቸዉን ሚና በመወጣት ላይ በመሆናቸዉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምስጋናዉን ያቀርባል፡፡

በ2014 የትምህርት ዘመን ማጠቃለያ ላይ ተማሪዎች ለትምህርታቸዉ ትኩረት ሰጥተዉ ከክፍል ክፍለ መዘዋወሪያ ማጠቃለያ ፈተናዎችን ለመውስድ እየተዘጋጁበት ባለበት ወቅት ላይ ማህበራዊ ሀላፊነት በጎደላቸው አካላት ሆን ተብሎ ተማሪዎችን ለማዘናጋት በዘንድሮ ዓመት ከክፍል ወደ ክፍል መዘዋወር የለም ተብሎ በማህበራዊ ምህዳሮች የሚናፈሰው ወሬ ፍፁም ከእውነት የራቀ እንዲሁም ከዚህ ጋር በተያያዘ ከኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር የወረደ አቅጣጫ የሌለ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ እያሳወቀ የትምህርት ባለድርሻ አካላት ተማሪዎች “ተማሪዎች ዘንድሮ በያላችሁበት ትደግማላቸሁ” በሚል አሉባልታ ሳይጠለፉ እና ሳይምታቱ ለትምህርታቸው ትኩረት ስጥተዉ ለተሻለ ውጤት እንዲተጉ እንድታደርጉ አደራ እንላለን፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s