ቀን 8/9/2014 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መምህራን ማህበር ለክፍለ ከተማ የማህበሩ አመራሮች የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት ጀመረ።

ስልጠናው ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀን የሚሰጥ ሲሆን በስልጠናው  በየዘርፉ በተከናወኑ ተግባራት እንዲሁም በማህበሩ መተዳደሪያ ደንብ ዙሪያ ውይይት እንደሚደረግ የተጠቀሰ ሲሆን በተጨማሪም አመራሮቹ ሙያዊ አቅማቸውን ማጎልበት በሚችሉባቸው የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ ስልጠና እንደሚሰጣቸው ተገልጿል።

በስልጠናው መክፈቻ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መምህራን ማህበር ፕሬዘዳንት አቶ ድንቅአለም ቶሎሳ እንዳስታወቁት ስልጠናው በክፍለ ከተማ ደረጃ የሚገኙ የማህበሩ ስራ አስፈጻሚዎች አቅማቸውን አጎልብተው የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት በአግባቡ መወጣት እንዲችሉ ታስቦ መዘጋጀቱን ገልጸው በተጨማሪም ስልጠናው የማህበሩ አመራሮች በየዘርፉ የሚያከናውኗቸውን የተለያዩ ተግባራት በማህበሩ መተዳደሪያ ደንብ መሰረት ማከናወን እንዲችሉ የሚያግዛቸውን ግንዛቤ ለማስጨበጥ እንደሚረዳቸውም አስገንዝበዋል።

ፕሬዘዳንቱ አክለውም ቀደም ብሎ የማህበሩ የከተማ ስራ አስፈጻሚዎች ተመሳሳይ ስልጠና መውሰዳቸውን  ጠቁመው የስልጠናው ተሳታፊዎችም በስልጠናው ያገኙትን ግንዛቤ መሰረት በማድረግ የማህበሩ መተዳደሪያ ደንብ እና ልዩ ልዩ መመሪያዎች በአግባቡ ተግባራዊ መደረጋቸውን ክትትል ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s