ቀን 29 /8/2014 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የስርዓተ ጾታ ማስረጽና ማካተት ዳይሬክቶሬት ለስርዓተ ጾታ ክበብ ተጠሪ መምህራን እና ለክፍለ ከተማ ዘርፈ ብዙ ባለሙያዎች ስልጠና ሰጠ።

የቢሮው የስርአተ ጾታ ማስረጽና ማካተት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሯ ወይዘሮ አበባ ዘውዴ በስልጠናው መክፈቻ ባስተላለፉት መልዕክት በትምህርት ቤቶች አከባቢ ተማሪዎችን ለተለያዩ ጾታዊ ጥቃቶች የሚያጋልጡ ጉዳዮች  አለመቀረፋቸውን ገልጸው እነዚህን አንገብጋቢ ችግሮች ለመቅረፍ በየትምህርት ቤቱ የተቋቋሙ የስርዓተ ጾታ ክበባት ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ስልጠናው ለክበብ ተጠሪ መምህራኑ ግንዛቤ መፍጠርን ታሳቢ አድርጎ መዘጋጀቱን አስታውቀዋል።

በዳይሬክቶሬቱ የስርዓተ ጾታ ማስረጽና ማካተት ባለሙያው አቶ ደረጀ ደምሴ በበኩላቸው በየትምህርት ቤቱ የሚገኙ የስርአተ ጾታ ክበብ ተጠሪ መምህራን በትምህርት ቤት አከባቢ የሚስተዋሉ ጾታዊ ጥቃቶችን ለመከላከል የሚያስችላቸውን እቅድ ማዘጋጀት እንዲችሉና  ያከናወኑዋቸውን ተግባራት ለሚመለከተው አካል በአግባቡ ሪፖርት ለማድረግ የሚያግዛቸውን ግንዛቤ ከስልጠናው እንደሚያገኙ ገልጸዋል።

ስልጠናውን ከትምህርት ሚኒስተር በመጡትና በዘርፉ የካበተ የማሰልጠን ልምድ ባላቸው አቶ እስክንድር ላቀው የተሰጠ ሲሆን የስልጠናው ተሳታፊዎችም የቀረቡ የስልጠና ርዕሰ ጉዳዮችን መሰረት በማድረግ ሰፊ ተሳትፎ አድርገዋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s