የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ምዝገባን አስመልክቶ ማብራሪያ ተሰጠ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት 12ኛ ክፍል ለሚያስፈትኑ የመንግስትና የግል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሀገር አቀፍ ፈተና የምዝገባ ስርዓትን አስመልክቶ ኦረንቴሽን ሰጥቷል::
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳኘው ገብሩ በገለፃው ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት በምዝገባው ወቅት የሚፈጠሩ የመረጃ ክፍተቶችን ለመከላከል በየደረጃው የሚገኝ አካል ለምዝገባው ትኩረት ሰጥቶ እንዲሰራ አሳስበዋል::
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዲናኦል ጫላ በበኩላቸው ክፍለ ከተሞችና የትምህርት ቤት ርዕሳነ መምህራን በምዝገባው ዝግጅት ሂደት የራሳቸው ሚና እንዳላቸው ገልፀዋል:: በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳም መረጃዎችን በአግባቡ በመሙላት ተመዝጋቢዎችን ዝግጁ እንዲያደርጉ አሳስበው በምዝገባ ሂደት መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ አብራርተዋል ::
በመድረኩ የፈተና እና አይ ሲ ቲ ባለሞያዎች ፣ የአማርኛና አፋን ኦሮሞ ትምህርት ቡድን መሪዎች እንዲሁም የትምህርት ቤት ርዕሳነ መምህራን ተገኝተዋል፡፡
በዘንድሮው ዓመት የ12ኛክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በ201 ትምህርት ቤቶች 50ሺ 504 ተማሪዎች በቀን ፣ በማታና በግል ይመዘገባሉ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ከሚያዝያ 7 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ምዝገባ እንደሚጀመር ከዳይሬክቶሬቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል::
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!
You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ…
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/
Website: – aaceb.gov.et
Email;- aacaebc@gmail.com
Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/
ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!
