ቀን 23 /7/2014 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማሻሻያ ለፍትሀዊነት(GEQIP -E)  የስራ ክፍል ፕሮግራሙን ተግባራዊ ከሚያደርጉ የስራ ክፍል ከተውጣጡ ባለሙያዎች ጋር በፕሮግራሙ አፈጻጸም ዙሪያ ውይይት አካሄደ።

የአጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማሻሻያ ለፍትሀዊነት (GEQIP) ፕሮግራም ከአለም ባንክና ከሌሎች ለጋሽ ሀገራት በሚመደብ በጀት ከ2002ዓ.ም ጀምሮ ላለፉት 13 አመታት የትምህርት ጥራትንና ተደራሽነትን ማሳደግ ላይ ትኩረት አድርጎ በመተግበር ላይ የሚገኝ ፕሮግራም መሆኑን የቢሮው የአጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማሻሻያ ለፍትሀዊነት ፕሮግራም አስተባባሪው አቶ አሸናፊ ከበደ አስታውቀዋል።

አስተባባሪው አክለውም ፕሮግራሙ ከ”ኦ” ክፍል ጀምሮ እስከ 12ኛ ክፍል ድረስ ባለው የትምህርት እርከን እንደሚተገበር ጠቁመው በዋናነትም ውስጣዊ የትምህርት ብቃትን ማሻሻል ፣ለልዩ ፍላጎት ተማሪዎች አገልግሎት የሚሰጡ የድጋፍ መስጫ ማዕከላትን ማደራጀት፣ የመማሪያ መጽሀፍትን ጨምሮ የተለያዩ ቁስቁሶችን ለትምህርት ቤቶች ድጋፍ የማድረግን ጨምሮ ለመምህራን ሙያዊ ብቃታቸውን የሚያሳድጉበትን ስልጠናዎች የመስጠት ስራ እንደሚሰራ አስገንዝበዋል።

የአጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማሻሻያ ለፍትሀዊነት (GEQIP-E) ፕሮግራም በአሁኑ ወቅት ሶስተኛ ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝና በጀቱም  ውጤትን መሰረት አድርጎ የሚለቀቅ እንደመሆኑ ፕሮግራሙ  የሚፈለገውን ውጤት ማምጣት እንዲችል ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት በትኩረት መስራት እንደሚጠበቅባቸው አቶ አሸናፊ አሳስበዋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s