ቀን 22/7/2014 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት በ2014 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ፎርም አሞላልና ተዛማጅ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ ከርዕሰ መምህራን ጋር ውይይት አካሄደ፡፡

በውይይቱ መክፈቻ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳኘው ገብሩ እንዳስታወቁት የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና የተማሪዎች ቀጣይ የህይወት ምዕራፍ የሚወሰንበት የትምህርት እርከን መሆኑን ጠቁመው ትምህርት ቤቶች የተፈታኝ ተማሪዎቻቸውን አጠቃላይ መረጃ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት በከፍተኛ ጥንቃቄ በመመዝገብ ለሚመለከተው አካል ማስተላለፍ እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዲናኦል ጫላ የ2014 ዓ.ም የአንደኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ምዝገባ እና የምዝገባ ቅጽ አጠቃቆርን የተመለከተ መመሪያ ያቀረቡ ሲሆን በመመሪያውም የተማሪዎች መረጃ ፣ የትምህርት ቤቶችና የክፍለ ከተሞች ኮድ፤ የተመዝጋቢ ተማሪዎች መብትና ግዴታ የሚሉና ሌሎች መሰል ጉዳዮች መካተታቸውን አስታውቀዋል፡፡፡፡

በውይይቱ ከአዲስ ከተማ ፣ አቃቂ ቃሊቲ ፣ አራዳ  ፣ ቦሌ ፣ ጉለሌ እንዲሁም ቂርቆስ ክፍለከተሞች የሚገኙ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሳነ መምህራን እና የክፍለከተሞቹ የሁለቱ ስርዓተ ትምህርት ትግበራ ቡድን መሪዎች ተሳታፊ ሲሆኑ በነገው እለትም ከቀሪ ክፍለ ከተማ ትምህርት ቤት ርዕሳነ መምህራኖች ጋር ተመሳሳይ ውይይት እንደሚደረግ ከስራ ክፍሉ ያገኘነው መረጃ ያሳያል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s