ቀን 20/7/2014 ዓ.ም

የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ትምህርት ፅህፈት ቤት በስራ አሰራር ስርዓት እና በአመለካከት ለውጥ ላይ ስልጠና መስጠቱን አስታወቀ፡፡

በውጤት አምጪ የስራ አሰራር ስርዓት እና በአመለካከት ለውጥ ዙሪያ በቂ ግንዛቤ ለመፍጠር ያስቻል ስልጠና ከትምህርት ቤቶች ለተወጣጡ 165 የቡድን መሪዎች ፣ ባለሙያዎች ፣ሱፐርቫይዘሮች ፣ ርዕሳነ መምህራን እና መምህራን መስጠቱን የክፍለ ከተማዉ ትምህርት ፅህፈት ቤት ሀላፊ የሆኑት ወይዘሪት ሙሉ አንዳርጌ ተናግረዋል፡፡

በውጤት አምጪ የስራ አሰራር ስርዓት እና በአመለካከት ለውጥ ዙሪያ ስልጠናው ያተኮረ እንደሆነ የጠቆሙት ሀላፊዋ በትምህርት ቤቶቻችን ውስጥ የተሻለ የስራ አሰራር ስርዓት ዘርግቶ ውጤታማ ከመሆን እና የተማሪዎቻችንን ውጤትና ስነ-ምግባር ከማሻሻል አኳያ ውስንነቶች በመታየታቸው ያንን ለመቅረፍም የተሰጠ ነው ብለዋል፡፡

ከአነዚህ ችግሮች በመውጣት አመለካከትን በማዘመን እና በውጤት አምጪ አሰራሮች ላይ ትኩረት ሰጥቶ በመስራት የትምህርት ስርዓቱ የሚፈልገውን ብቁ ዜጋ ማፍራት እና ለሀገር ልማት እድገት ሚናውን የሚወጣ ትውልድ ለመቅረፅ የሚደረገውን ጥረትንም ስልጠናዉ ይደግፋል ተብሏል፡፡

የተማሪዎችን ውጤትና ስነ-ምግባር ለማሻሻል የሁሉም ባለድርሻ አካላትን የጋራ ርብርብ የሚጠይቅ ነው ያሉት ሀላፊዋ በዘርፉ ላይ የሚሰሩና በባለ ድርሻነት እየተሳተፉ ያሉ አካላት ጭምር በጋራ መስራት ወሳኝነት ይኖረዋል ብለዋል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s