ቀን 29/6/2014 ዓ.ም

ማርች 8 ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ተከበረ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሰራተኞች ማርች 8 ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን በተለያዩ መርሃ ግብሮች አክብረዋል፡፡

የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ስርዓተ ፆታ ማስረፅና ማካተት ዳይሬክቶሬት ዕለቱን በማስመልከት ባዘጋጀው በዓል ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሲሳይ እንዳለ ቀኑን በማስመልከት ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር  የሴቶች ቀንን ስናከብር ከእለት ወደ እለት እየተሻሻለ የመጣውን የሴቶች ተሳትፎና ክብር መስጠት ማጠናከርና ለሴቶች ድጋፍ በማድረግ አጋርነታችንን ማሳየት አለብን ሲሉ ገለፀዋል ::

ለሀገር ልማትና ሠላም መረጋገጥ የሴቶች ተሳትፎ ትልቅ እንደሆነ የገለፁት የፅህፈት ቤት ኃላፊው ሴቶች ስለሚችሉ በብቃት ተወዳድረው ባገኙት የስራ እድል ሁሉ ስኬታማ መሆን እንደቻሉ ማረጋገጥ የቻልንበት ጊዜ ነው ብለዋል ::

በወቅቱ ማርች 8 ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ሆኖ የሚከበርበት አላማና : የሴቶች እኩልነት መብትን የሚያሳዩ የኢትዮጵያ ሕግ አንቀፆችና ለግንዛቤ ማስጨበጫ ሰነድ ቀርቧል ::

ቀኑን በማስመልከትም ጥያቄና መልስ ውድድርና ግጥሞች ቀርበዋል ::

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አባልና እጩ ዶክተር ወ /ሮ አቶሜ አበበ በፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው የሕይወት ልምዳቸውን አካፍለዋል :: በመድረኩ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በዓለም አቀፍ ለ 111ኛ  በሀገራችን ለ46ኛ ጊዜ እየተከበረ እንዳለ ተመላክቷል ::

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s