ቀን 24/6/2014 ዓ.ም

የተማሪዎች የመማሪያ መጽሀፍና የመምህር መምሪያ ግምገማ ውጤታማ መሆኑ ተገለፀ ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አዲሱን ስርዓተ ትምህርት መሰረት አድርጎ ተዘጋጅቶ በተመረጡ ትምህርት ቤቶች በሙከራ ደረጃ ተግባራዊ የተደረገው የተማሪዎች የመማሪያ መጽሀፍና የመምህር መምሪያ ግምገማ  የደረሰበት ደረጃ የተገመገመ ሲሆን በመድረኩ ግምገማው በሚጠበቀው ደረጃ በመከናወኑ  ውጤታማ  ግምገማ መሆኑ ተገልፃል፡፡  ፡፡

የመጽሀፍ ግምገማው የደረስበትን ደረጃ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ አቶ ዘላለም ሙላቱ ፣ የቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊ አቶ ሳምሶን መለሰ እና የቢሮ ጽፈት ቤት  ሀላፊ አቶ ሲሳይ እንዳለ በመገኘት ገምግመዋል።

እየተካሄደ ያለውን የተማሪዎች የመማሪያ መጽሀፍም ሆነ የመምህር መምሪያ የመጽሀፍ ግምገማ የደረሰበትን ደረጃ አስመልክቶ እስካሁን ባለው ሂደት ገምጋሚ መምህራኑ በተዘጋጀላቸው የመገምገሚያ መስፈርት መጽሀፍቱን በወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት በአግባቡ በመገምገም የማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ መድረሳቸው የግምገማውን ውጤታማነት የሚያሳይ መሆኑ ተመላክቷል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ አቶ ዘላለም ሙላቱ በቀጣይ ግምገማዉ ላይ የተነሱ ጉዳዮችን በማካተት ፤ የማጠቃለያ ስራዎችን በመከወን እና የጋራ የምክክር መድረክ በማከናወን የስራዉን ውጤታማነት ከዚህ የበለጠ ለማጎልበት መስራት እንደሚገባ አቅጣጫ ሰጥተዋል፡፡

የመጽሀፍ ግምገማው ከ17/06/2014 ዓ.ም ጀምሮ ለአንድ ሳምንት የሙከራ ትግበራው ከሚካሄድባቸው  ትምህርት ቤቶች  በተመረጡ መምህራንና በመጽሀፍ ዝግጅቱ ተሳታፊ በነበሩ መምህራን እንዲሁም በቢሮው የስርዓተ ትምህርት ዝግጅትና ትግበራ ባለሙያዎች በየትምህርት አይነቱ በአማርኛ እና አፋን ኦሮሞ ቋንቋዎች በእቴጌ መነን የሴት ተማሪዎች  አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ አዳሪ ትምህርት ቤት በመካሄድ ላይ መሆኑ ይታወቃል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ

Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: – http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: – aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: – https://www.instagram.com/aacaeb/

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s